Co.Market / ኮ-ገበያ
551 subscribers
5.06K photos
81 videos
3 files
2.47K links
  📲+251 9 11 81 16 72
https://ermitheethiopia.com

👉
Download Telegram
Forwarded from Ermi The Ethiopia
Full furnished apartment for rent
Contact :- Ermi the Ethiopia
                  09 44 36 59 59
                    @ErmiTE5959
1
Forwarded from Ermi The Ethiopia
ስድስተኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ የመጨረሻዎቹ አሸናፊ ተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ።

ነሀሴ 23/12017 (መልአ)
------------------------------------------------
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት የህብረተሰቡን የመሬት ፍላጎት መነሻ በማድረግ በየሶስቱ ወሩ ግልጽና ነፃ የሆነ የመሬት ሊዝ ጨረታ እያወጣ ይገኛል።

ቢሮው በተያዘው አዲሱ በጀት ዓመትም መሬትን ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸው ፕሮጀክቶች ከማቅረብ ጎን ለጎን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ባሳተፈ መልኩ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለማስተላለፍ ይረዳ ዘንድ በሰባት ክፍለ ከተሞች 132 ፕሎቶች የያዘውን 6ኛውን ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ከነሀሴ 13/2017 እስከ ነሀሴ 15/2017 ተጫራቶችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሲካሄድ ቆይቶ በየእለቱ የአሽናፊዎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማደረጉ ይታወቃል።

ይህን ተከትሎ በሊዝ ጨረታ መመሪያ መሰረት የጨረታው አሽናፊዎች ጊዜያዊ ውጤት በአጠረ ጊዜ ውስጥ ተገቢው ማጣሪያ ተደርጎበት የመጨረሻዎቹ አሸናፊ ተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝር በቢሮው እስትራቴጅክ ካውንስል ፀድቋል ።

የዚህን ዝርዝር ሙሉ ሀሳብ ነገ ነሀሴ 24/2017 ታትሞ በሚወጣው በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ላይ የሚያገኙት ሲሆን በጋዜጣው ላይ በተዘረዘረዉ አግባብ 1ኛ የወጣችሁ አሸናፊ ተጫራቾች ይህ ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር(10) የስራ ቀናት ዉስጥ ለም ሆቴል አካባቢ ኤም.ኤ.ህንጻ ላይ በሚገኘዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 303 በመቅረብ የሚጠበቅባችሁን በማሟላት የሊዝ ዉል እንድትፈጽሙ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።

በዚህ መሰረት 1ኛ የወጣችሁ አሸናፊ ተጫራቾች በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቀርባችሁ ዉል የማትፈጽሙ ከሆነ በሊዝ ደንቡ መሰረት ዕድሉ 2ኛ ለወጡ ተጫራቾች የሚሰጥ በመሆኑና 2ኛ የወጡ ተጫራቾችም በተመሳሳይ ዉል የማይፈጽሙ ከሆነ 3ኛ የወጡ ተጫራቾች በሊዝ ደንብ 162/2016 እና በተጫራቾች መመሪያ ላይ በተቀመጠዉ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በዉስጥ ማስታወቂያ ጥሪ እንደሚደርግም ተገልጿል ።

ለጨረታ ከወጡ 132 ቦታዎች ዉስጥ በተደረገው የመጨረሻ ማጣሪያ የቦታ ኮድ LDR-NIF-MIX-00014508 ከጨረታ የተሰረዘ ስለመሆኑም የቢሮው የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ከጨረታ ኮሚቴው ያገኘው መረጃ ያመላከታል፡፡
2