Co.Market / ኮ-ገበያ
537 subscribers
5.06K photos
81 videos
3 files
2.47K links
  📲+251 9 11 81 16 72
https://ermitheethiopia.com

👉
Download Telegram
አርቲስት ተዘራ ለማ በድንገተኛ የልብ ህመም ህይወቱ አለፈ!

አርቲስት ተዘራ ለማ እስካሁን ከ20 በላይ ፊልሞች ላይ የተለያዩ ገፀ ባህሪያትን ተጫውቷል። ውሳኔ፣ ከኩርባው በስተጀርባ፣ ፍቅር ባጋጣሚ ፣ታሰጨርሺኛለሽ፣ ፍቅር በይሉኝታ፣ አልወድሽም፣ ወንድሜ ያዕቆብ፣ ኢንጂነሩ፣ ጥቁር እና ነጭ፣ ፍፃሜው፣ ሀማርሻ፣ ሰውዬው፣ የፍቅር ቃል፣ ቪዳ፣ ባዶ ነበር፣ ፀሀይ የወጣች ቀን፣ ጣምራ፣ የበኩር ልጅ፣ እሷን ብዬ፣ ጉደኛ ነች፣ ሰበበኛ፣ ዘውድና ጎፈር ፤ በመሰራት ላይ ያሉ እና በቅርብ የሚወጡ ታላቁ ሩጫ ፣ ሰንሰለት ፣ እስክትመጪ ልበድ እና ሌሎችም ይጠቀሳሉ።

በ “በኩር ልጅ” ፊልምም ባሳየው የገፀ ባህሪይ አጨዋወት በ9ኛው የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ላይ “የአመቱ ምርጥ ተዋናይ” ተብሎ ተሸልሟል። በ”ፍቅር ቃል” ፊልም ላይም እንዲሁ ባሳየው ብቃት ከእነ ቤተሰቡ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።

በ1954ዓ.ም ፍቼ የተወለደው አርቲስት ተዘራ ለማ እድገቱ እዚሁ መዲናችን አዲስ አበባ ርቼ አካባቢ ነው ይህ አርቲስት ወደ ጥበቡ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በፊልም፣ በቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ ፣ በትያትር እና በልዩ ልዩ ማስታወቂያዎች ላይ ሰርቷል። በተወለደ በ57 አመቱ አርቲስት ተዘራ ለማን በድንገተኛ ህመም ከእዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

ኢትዮ_fiction ለዚህ የጥበብ ሰው ነፍስ ይማር እያለች ለቤተሰቡም መፅናናትን ትመኛለች ።

ምንጭ:- Etv
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
❗️❗️ሰበር ዜናናናና❗️❗️

✔️የ10ኛ ክፍል ውጤት በመላ ሀገሪቱ ይፋ ሆኗል

👉ውጤታችሁን በየትኛውም አካባቢ በያላቹበት ሆናችሁ ያለምንም Internet መጨናነቅ linkun በመንካት ተመልከቱ

👉 https://t.me/joinchat/AAAAAEZh0QTYoIsKmuxHBQ 👈
17 የምግብ ዘይት ምርት አይነቶች መሠረታዊ ችግር ስላለባቸው ኅብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማሳሰቢያ ተሰጠ፡፡

የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በአዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች ባደረገው የገበያ ጥናት በ17 የምግብ ዘይት ምርቶች ላይ መሠረታዊ ችግር ስላለባቸው ኅብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው አሳስቧል፡፡

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ባደረገው የገበያ ጥናት የዘይት ምርቶቹ የሚመረቱበት ቦታና የተመረተበት ሀገር፣ የምርት መለያ ቁጥር፣ የአምራች አድራሻ የሌላቸው፣ የገላጭ ጽሁፍ ችግር ያለባቸው መሆንና ለጤና ጠቀሜታ እንዳለው ተደርጎ የተቀመጡ መሆን፣ የመጠቀሚያ ጊዜና ማብቂያ ቀን የሌላቸው እንደሆኑ አስታውቋል። የሀገሪቱን የደረጃ ምልክት ያልለጠፉና ደረጃውንም የማያሟሉ መሆናቸው በተደረገው ጥናት መረጋገጥ መቻሉን ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡

እነዚህም የምግብ ዘይት ምርቶች፦ ሉሉ ዘይት፣ አርሲ ዘይት፣ አሃዱ ዘይት፣ ድሬ ንጹህ የምግብ ዘይት፣ አሚን ንጹህ የምግብ ዘይት፣ ሮያል የምግብ ዘይት፣ ዳግም የተጣራ የኑግ ዘይት፣ ጄጃን የምግብ ዘይት፣ ውብ የተጣራ የኑግ ዘይት፣ ለማ የኑግ ዘይት፣ ኑድ ንጹህ የምግብ ዘይት፣ ገበታ የምግብ ዘይት፣ ዘመን ዘይት፣ አጋር ዘይት፣ አናጅ ዘይት፣ ሳባ ዘይት እና ጃሎ ዘይት ናቸው።

የተጠቀሱትን ምረቶች ኅብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው በጥብቅ አሳስቧል።