🚨 #አዲሱ_የካሳ_ህግ_ማብራሪያ ⁉️⤵️
አዲሱ የካሳ አዋጅ ቁጥር 1161/2012 አንቀጽ 2(2) የንብረት ካሳ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት ወይም ላደረገው ቋሚ ማሻሻያ በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል።
#ቋሚ ማሻሻያ ማለት በይዞታው ላይ የሚሰራ የምንጣሮ፣ ድልደላ እርከን ስራ፣ ውሃ የመከተር ስራ እና የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉት ስራዎች ይጠቃለላል በማለት ይደነግጋል ፡፡ በመሆኑም አዲሱ አዋጅ የተሻለ ነገር ይዞ የመጣው ካሳ የሚከፈለው ለሰፈረ ንብረት እና ለተደረገ ቋሚ ማሻሻል እንደሆነ ይደነግጋል፡፡
#ቋሚ ማሻሻል የሚለው አሁንም ሌላ ውዝግብ የሚያስነሳ ነው ምክንያቱም ከተዘረዘሩት ድርጊቶች ውጪ ያደረገው ለምሳሌ መሬት በተለያየ መንገድ ለም እንዲሆን፣ ምርታማ እንዲሆን የሰራው ስራ በየትኛው ነው ሚካተተው? ምንጣሮ ነው?
#አዲሱ_ አዋጅ_የያዛቸው_ትሩፋቶች
(1) #የቀዳሚነት መብት፡-
ቀድሞ በነበረው አዋጅ 455/97 ያልነበረ ነገር ግን አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አካቶ ያወጣው ሰዎች ቀድሞ ለፍተው ባለሙት የመሬት ይዞታቸው አቅም ያላቸው በሆኑ ጊዜ በከተማ ፕላን መሰረት ለብቻቸው ወይም በጣምራ ማልማት የሚችሉበት የቀዳሚነት መብት በአንቀጽ 7 ስር ማጎናፀፋ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(2) #ካሳ የማግኘት መብት:-
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አንቀፅ 8(1)(ሰ) ስር የልማት ተነሺውን ማስነሳት የሚቻለው ለተነሺው ካሳ ከተፈለ እና ምትክ ቦታ ወይም ቤት ከሰጠ በኋላ መሆን እንዳለበት አዋጁ ይደነግጋል፡፡በመሆኑም ሰዎች በይዞታቸው ካሳም ሳይከፈላቸው ምትክ ቦታም ሳይሰጣቸው እንዲነሱ ተደርጎ የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው የነበሩ ባለይዞታዎች በጣም ብዙ የነበሩ በመሆኑ ይህ አዋጅ ህዝቡ ውስጥ የነበረው ችግር ለመፍታት ተነሺዎች ከመነሳታቸው በፊት አስቀድመው ካሳ እና ምትክ ቦታ ማግኘት እንዳለባቸው መደንገጉ በሕግ ደረጃም ቢሆን ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(3) #ካሳ በወቅቱ ካልተከፈላቸው መልሶ የመያዝ መብት
ተነሺዎች የካሳ ግምት በጹሑፍ እንዲያውቁ ከተደረገ ቀን ጀምሮ በሶስት ወር ውስጥ ካሳ ካልተከፈላቸው በመሬት ይዞታቸው ከቋሚ ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሳ ካልተከፈው በፕላን የሚፈቀድ እና ቀጣይ የቦታውን የልማት ወጪ በመንግስት ላይ የማያበዛ በመሬቱ ላይ ማንኛውም ስራ መስራት ይችላል በማለት ይደነግጋል።
ቢሆንም ግን ይህ ድንጋጌ እጅግ አሻሚ ነው ምክንያቱም መንግስት ካሳ ካልከፈለ በፕላን መሰረት ባለይዞታ ማንኛውንም ዓይነት ስራ መስራት እንደሚችል ከተደነገገ በኋላ በመንግስት የልማት ወጪ የማያበዛ ስራ ማለቱ ምን ማለት ነው? እጅግ በጣም ግልጽ ነት የጎደለው ነው፡፡
(4) #ተመጣጣኝ ካሳ ክፍያና ምትክ ቦታ
አዲሱ አዋጅ በመሬቱ ላይ ለተፈራ ንብረት፣ ቋሚ ማሻሻያ ባለይዞታው ንብረቱን ማዘዋወር የሚችል ከሆነ የማዘዋወሪያ ወጪ ወይም የትራንስፖርት/የማጓጓዣ ወጪ ከመክፈሉ በተጨማሪ ከገጠር መሬት ይዞታ ለሚነሳ የመሬት በላይዞታ ተነሺ ከተወሰደበት መሬት ተመጣጣኝ የሆነ ምትክ መሬት እና መሬት ይዞታው ከመልቀቅ በፊት ባሉ ሶስት ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ምርት ያመረተበትን ምርት በወቅታዊ ዋጋ ተሰልቶ በ15 ተባዝቶ ይከፈላል በማለት ይደነግጋል፡፡
(5) #በአዋጅ አንቀጽ 2(4) የልማት ተነሽ ድጋፍ የመሬት ባለይዞታ ከመሬቱ በጊዜያዊም ሆነ በቋሚነት ሲነሳ ከአዲሱ አከባቢ ጋር መላመድ እንዲችል ከንብረት እና ከልማት ተነሽ ካሳ በተጨማሪ በዓይነት ወይም በገንዘብ የሚሰጥ ድጋፍ ነው፡፡ it is promising move አዲስ እና በጣም ጥሩ የሚባል ነው ነገር ግን ይህ ነገር የሚወሰነው በክልሎች መመሪያ ነው፣ መች ይሁን የሚወጣው? ባይወጣስ?
(6) #የወል ይዞታዎች ላይ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
በእርግጥ ወል ይዞታና የመንግስት የወል የተቀላቀለ በመሆኑ በወል ይዞታዎች ላይ ካሳ ሲከፈል አይታይም፣ በዚህ አዋጅ የወል ይዞታ ማለት ከመንግስት ወይም ከግል ይዞታነት ውጭ የሚገኝና የአከባቢው ማህበረሰብ ለግጦሽ፣ ለደንና ለማህበራዊ አገልግሎት በጋራ የሚጠቀሙበት የመሬት ይዞታ ነው በማለት አንቀፅ 2(11) ይደነግጋል።
በመሆኑ የወል ይዞታዎች አገኘን ተብሎ በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካል መሸንሸን አይችሉም ማለት ነው፡፡ የወል መሬቱ የካሳ ስሌት የወል መሬቱ ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወይም ጥቅሙ የቀረባቸውን የአኗኗር ዘይቤ ወይም መተዳደሪያ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ማለት ነው? አሁንም ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡የወል መሬቱ የተወሰደባቸው የወል መሬቱ ተጠቃሚ አካል የተገኘው ገንዘብ ለማህበረሰቡ አባላት እኩል ሊካፈል ወይም በዓይነት ሊጠቀሙበት የሚችሉበትን መንገድ መቅረጽ አለበት በማለት አንቀፅ 13(3) ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የወል መሬት ያለካሳ የሚወስድ የመንግስት አካል ከድርጊቱ መቆጠብ አለበት፡፡
(7) #የልማት ተነሺ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
የከተማ መሬት ባለይዞታ ከይዞታው በቋሚነት ተነሽ በሚሆንበት ጊዜ የሚከፈለው የልማት ተነሺ ካሳ እና የሚሰጠው ምትክ ቦታ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡
የልማት ተነሺ ካሳ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡ይህ አይነቱ ካሳ የመጠቀም መብት በመኖሩ ብቻ የሚገኝ የካሳ ዓይነት ነው፡፡ ለከተማ ተነሺ በአከባቢ ለነበረው የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና ለሚደርሰው የስነ-ልቦና ጉዳት ማካካሻ ይከፈለዋል መጠኑ በደንብ ይወሰናል 13(4)(ሠ) በማለት ይደነግጋል፡፡
ግን ይህ ካሳ በተግባር ተከፍሎ አያውቅም። #የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስ-ልቦና ጉዳት ካሳ ማለት ለተጎጂ ከነበረበት አከባቢ በመነሳቱ የነበረው ማህበራዊ ትስስር በመቋረጡ የሚከፈል የጉዳት ማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
በመሆኑም በከተማ መሬት ይዞታ የሚነሳ ሰው የልማት ተነሺነት ካሳ፣ምትክ ቦታ፣ቤት ፈርሶበት ከሆነ የቤት መስሪያ ዋጋና በቦታው እስኪገባ ባለው 2 ዓመት የሚኖርበት ቤት ወይም የወቅታዊ የኪራይ ገንዘብ ግምት እና የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስነ-ልቦና ጉዳት ካሳ ይከፍለዋል፡፡በመሆኑም እነዚህ መብቶች በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ ጥሩና ተስፋ ሰጪ የመሬት ካሳ መብቶች ናቸው፡፡
#መልሶ ማቋቋም ፡- በአዋጅ አንቀጽ 16 የክልል መንግስት ወይም የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ አስተዳደር ለካሳ ክፍያ እና ለመልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቋቁማል በማለት ይደነግጋል፡፡ መልሶ ማቋቋም ማለት በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ የሚያስችል የሚሰጥ ድጋፍ ነው ። ጥያቄው ግን መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ባይቋቋምስ ❓ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሰት እርከን ካሳን በሚመለከት አቤቱታ የሚሰማ ኮሚቴ አንኳን አላቋቋሙም መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቁማሉ ❓
አዲሱ የካሳ አዋጅ ቁጥር 1161/2012 አንቀጽ 2(2) የንብረት ካሳ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት ወይም ላደረገው ቋሚ ማሻሻያ በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል።
#ቋሚ ማሻሻያ ማለት በይዞታው ላይ የሚሰራ የምንጣሮ፣ ድልደላ እርከን ስራ፣ ውሃ የመከተር ስራ እና የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉት ስራዎች ይጠቃለላል በማለት ይደነግጋል ፡፡ በመሆኑም አዲሱ አዋጅ የተሻለ ነገር ይዞ የመጣው ካሳ የሚከፈለው ለሰፈረ ንብረት እና ለተደረገ ቋሚ ማሻሻል እንደሆነ ይደነግጋል፡፡
#ቋሚ ማሻሻል የሚለው አሁንም ሌላ ውዝግብ የሚያስነሳ ነው ምክንያቱም ከተዘረዘሩት ድርጊቶች ውጪ ያደረገው ለምሳሌ መሬት በተለያየ መንገድ ለም እንዲሆን፣ ምርታማ እንዲሆን የሰራው ስራ በየትኛው ነው ሚካተተው? ምንጣሮ ነው?
#አዲሱ_ አዋጅ_የያዛቸው_ትሩፋቶች
(1) #የቀዳሚነት መብት፡-
ቀድሞ በነበረው አዋጅ 455/97 ያልነበረ ነገር ግን አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አካቶ ያወጣው ሰዎች ቀድሞ ለፍተው ባለሙት የመሬት ይዞታቸው አቅም ያላቸው በሆኑ ጊዜ በከተማ ፕላን መሰረት ለብቻቸው ወይም በጣምራ ማልማት የሚችሉበት የቀዳሚነት መብት በአንቀጽ 7 ስር ማጎናፀፋ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(2) #ካሳ የማግኘት መብት:-
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አንቀፅ 8(1)(ሰ) ስር የልማት ተነሺውን ማስነሳት የሚቻለው ለተነሺው ካሳ ከተፈለ እና ምትክ ቦታ ወይም ቤት ከሰጠ በኋላ መሆን እንዳለበት አዋጁ ይደነግጋል፡፡በመሆኑም ሰዎች በይዞታቸው ካሳም ሳይከፈላቸው ምትክ ቦታም ሳይሰጣቸው እንዲነሱ ተደርጎ የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው የነበሩ ባለይዞታዎች በጣም ብዙ የነበሩ በመሆኑ ይህ አዋጅ ህዝቡ ውስጥ የነበረው ችግር ለመፍታት ተነሺዎች ከመነሳታቸው በፊት አስቀድመው ካሳ እና ምትክ ቦታ ማግኘት እንዳለባቸው መደንገጉ በሕግ ደረጃም ቢሆን ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(3) #ካሳ በወቅቱ ካልተከፈላቸው መልሶ የመያዝ መብት
ተነሺዎች የካሳ ግምት በጹሑፍ እንዲያውቁ ከተደረገ ቀን ጀምሮ በሶስት ወር ውስጥ ካሳ ካልተከፈላቸው በመሬት ይዞታቸው ከቋሚ ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሳ ካልተከፈው በፕላን የሚፈቀድ እና ቀጣይ የቦታውን የልማት ወጪ በመንግስት ላይ የማያበዛ በመሬቱ ላይ ማንኛውም ስራ መስራት ይችላል በማለት ይደነግጋል።
ቢሆንም ግን ይህ ድንጋጌ እጅግ አሻሚ ነው ምክንያቱም መንግስት ካሳ ካልከፈለ በፕላን መሰረት ባለይዞታ ማንኛውንም ዓይነት ስራ መስራት እንደሚችል ከተደነገገ በኋላ በመንግስት የልማት ወጪ የማያበዛ ስራ ማለቱ ምን ማለት ነው? እጅግ በጣም ግልጽ ነት የጎደለው ነው፡፡
(4) #ተመጣጣኝ ካሳ ክፍያና ምትክ ቦታ
አዲሱ አዋጅ በመሬቱ ላይ ለተፈራ ንብረት፣ ቋሚ ማሻሻያ ባለይዞታው ንብረቱን ማዘዋወር የሚችል ከሆነ የማዘዋወሪያ ወጪ ወይም የትራንስፖርት/የማጓጓዣ ወጪ ከመክፈሉ በተጨማሪ ከገጠር መሬት ይዞታ ለሚነሳ የመሬት በላይዞታ ተነሺ ከተወሰደበት መሬት ተመጣጣኝ የሆነ ምትክ መሬት እና መሬት ይዞታው ከመልቀቅ በፊት ባሉ ሶስት ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ምርት ያመረተበትን ምርት በወቅታዊ ዋጋ ተሰልቶ በ15 ተባዝቶ ይከፈላል በማለት ይደነግጋል፡፡
(5) #በአዋጅ አንቀጽ 2(4) የልማት ተነሽ ድጋፍ የመሬት ባለይዞታ ከመሬቱ በጊዜያዊም ሆነ በቋሚነት ሲነሳ ከአዲሱ አከባቢ ጋር መላመድ እንዲችል ከንብረት እና ከልማት ተነሽ ካሳ በተጨማሪ በዓይነት ወይም በገንዘብ የሚሰጥ ድጋፍ ነው፡፡ it is promising move አዲስ እና በጣም ጥሩ የሚባል ነው ነገር ግን ይህ ነገር የሚወሰነው በክልሎች መመሪያ ነው፣ መች ይሁን የሚወጣው? ባይወጣስ?
(6) #የወል ይዞታዎች ላይ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
በእርግጥ ወል ይዞታና የመንግስት የወል የተቀላቀለ በመሆኑ በወል ይዞታዎች ላይ ካሳ ሲከፈል አይታይም፣ በዚህ አዋጅ የወል ይዞታ ማለት ከመንግስት ወይም ከግል ይዞታነት ውጭ የሚገኝና የአከባቢው ማህበረሰብ ለግጦሽ፣ ለደንና ለማህበራዊ አገልግሎት በጋራ የሚጠቀሙበት የመሬት ይዞታ ነው በማለት አንቀፅ 2(11) ይደነግጋል።
በመሆኑ የወል ይዞታዎች አገኘን ተብሎ በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካል መሸንሸን አይችሉም ማለት ነው፡፡ የወል መሬቱ የካሳ ስሌት የወል መሬቱ ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወይም ጥቅሙ የቀረባቸውን የአኗኗር ዘይቤ ወይም መተዳደሪያ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ማለት ነው? አሁንም ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡የወል መሬቱ የተወሰደባቸው የወል መሬቱ ተጠቃሚ አካል የተገኘው ገንዘብ ለማህበረሰቡ አባላት እኩል ሊካፈል ወይም በዓይነት ሊጠቀሙበት የሚችሉበትን መንገድ መቅረጽ አለበት በማለት አንቀፅ 13(3) ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የወል መሬት ያለካሳ የሚወስድ የመንግስት አካል ከድርጊቱ መቆጠብ አለበት፡፡
(7) #የልማት ተነሺ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
የከተማ መሬት ባለይዞታ ከይዞታው በቋሚነት ተነሽ በሚሆንበት ጊዜ የሚከፈለው የልማት ተነሺ ካሳ እና የሚሰጠው ምትክ ቦታ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡
የልማት ተነሺ ካሳ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡ይህ አይነቱ ካሳ የመጠቀም መብት በመኖሩ ብቻ የሚገኝ የካሳ ዓይነት ነው፡፡ ለከተማ ተነሺ በአከባቢ ለነበረው የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና ለሚደርሰው የስነ-ልቦና ጉዳት ማካካሻ ይከፈለዋል መጠኑ በደንብ ይወሰናል 13(4)(ሠ) በማለት ይደነግጋል፡፡
ግን ይህ ካሳ በተግባር ተከፍሎ አያውቅም። #የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስ-ልቦና ጉዳት ካሳ ማለት ለተጎጂ ከነበረበት አከባቢ በመነሳቱ የነበረው ማህበራዊ ትስስር በመቋረጡ የሚከፈል የጉዳት ማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
በመሆኑም በከተማ መሬት ይዞታ የሚነሳ ሰው የልማት ተነሺነት ካሳ፣ምትክ ቦታ፣ቤት ፈርሶበት ከሆነ የቤት መስሪያ ዋጋና በቦታው እስኪገባ ባለው 2 ዓመት የሚኖርበት ቤት ወይም የወቅታዊ የኪራይ ገንዘብ ግምት እና የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስነ-ልቦና ጉዳት ካሳ ይከፍለዋል፡፡በመሆኑም እነዚህ መብቶች በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ ጥሩና ተስፋ ሰጪ የመሬት ካሳ መብቶች ናቸው፡፡
#መልሶ ማቋቋም ፡- በአዋጅ አንቀጽ 16 የክልል መንግስት ወይም የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ አስተዳደር ለካሳ ክፍያ እና ለመልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቋቁማል በማለት ይደነግጋል፡፡ መልሶ ማቋቋም ማለት በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ የሚያስችል የሚሰጥ ድጋፍ ነው ። ጥያቄው ግን መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ባይቋቋምስ ❓ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሰት እርከን ካሳን በሚመለከት አቤቱታ የሚሰማ ኮሚቴ አንኳን አላቋቋሙም መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቁማሉ ❓
https://ermitheethiopia.com/listing/condominium-for-sale-in-addis-ababa-code-jb-349/?doing_wp_cron=1630945728.2402210235595703125000
Condominium for sale in addis ababa code-JB- 349
Condominium for sale in addis ababa code-JB- 349
https://ermitheethiopia.com/listing/g1-residential-building-for-rent-code-ap-350/?doing_wp_cron=1630946865.4354000091552734375000
G+1 Residential building for Rent code-AP- 350
G+1 Residential building for Rent code-AP- 350
https://ermitheethiopia.com/listing/toyota-hilux-for-sale-in-addis-ababa-code-ab-351/
Toyota hilux for sale in addis Ababa code- AB-351
Toyota hilux for sale in addis Ababa code- AB-351
https://ermitheethiopia.com/listing/new-villa-house-for-sale-in-addis-ababa-code-yk-348/?doing_wp_cron=1630949110.4426400661468505859375
New villa house for sale in addis ababa code-YK- 348
New villa house for sale in addis ababa code-YK- 348
https://ermitheethiopia.com/listing/brand-new-apartment-for-rent-around-bole-code-ap-352/?doing_wp_cron=1631031159.5012769699096679687500
Brand new apartment for rent around bole code-AP-352
Brand new apartment for rent around bole code-AP-352
https://ermitheethiopia.com/listing/apartments-guest-house-for-rent-around-kazanchis-code-ap-353/?doing_wp_cron=1631033353.4657111167907714843750
Apartments Guest house for rent around Kazanchis code-AP-353
Apartments Guest house for rent around Kazanchis code-AP-353
https://ermitheethiopia.com/listing/hoyundia-atoz-for-sale-in-addis-ababa-code-al-354/?doing_wp_cron=1631101023.4888949394226074218750
Hoyundia atoz for sale in addis ababa code -AL- 354
Hoyundia atoz for sale in addis ababa code -AL- 354
https://ermitheethiopia.com/listing/toyota-hilux-double-cab-for-sale-in-addis-ababa-code-jb-355/?doing_wp_cron=1631102663.5048739910125732421875
Toyota hilux double cab for sale in addis ababa code-JB- 355
Toyota hilux double cab for sale in addis ababa code-JB- 355
https://ermitheethiopia.com/listing/suzuki-every-for-sale-in-addis-ababa-code-al-356/?doing_wp_cron=1631115569.0415999889373779296875
Suzuki Every for sale in addis ababa code -AL- 356
Suzuki Every for sale in addis ababa code -AL- 356
https://ermitheethiopia.com/listing/new-villa-house-for-sale-code-jb-357/?doing_wp_cron=1631124959.7277851104736328125000
New villa house for sale code-JB- 357
New villa house for sale code-JB- 357
https://ermitheethiopia.com/listing/apartments-guest-house-around-bole-code-ap-343/?doing_wp_cron=1631125276.6514079570770263671875
Apartments Guest house around bole code-AP- 344
Apartments Guest house around bole code-AP- 344