የኛ ግጥም
44 subscribers
2 photos
2 links
#Kehas

#For business

#gitm

#Tarik

#Feta 😁

#Zena😍

#Sak😀

#desta😇
Download Telegram
​​🌺የከንቲባው ልጅ 🌺

🔥ክፍል 35
.
ጠዋት እንደተለመደው ወደ ክፍል ሄጄ እስከ ምሳ ሰዓት ተምረን ፣ ቶኒ ምሳ በልተን ወደ ዶርም ገባሁ ። Telegram መጠቀም በጣም ስለምወድ ስልኬን አወጣሁና ገባሁ ። ትናንት በተላከልኝ ፣ መልሼ ስደውል እምቢ ባለኝ ስልክ ቁጥር አዲስ መልዕክት ተላከልኝ ። "እንዴት ነህ የኔ ጌታ ፡ በመጀመሪያ የሚያናድድህ ነገር አድርጌ ከሆነ በጣም ይቅርታ ። ትናንት ያንን መልዕክት እኔ ነኝ አዲስ ሲም ካርድ አውጥቼ የኩልህህ ። ሁለት ልብ ሆነህ ሳይክ በመሀል ተጨነኩና እንዲቆርጥልህ ብዬ እንደዛ አደረኩ ። ስለ ፍቅር ካንተ አንድ የተማርኩት ትልቅ ነገር ቢኖር 'እራስ ወዳድ መሆን የለብንም' የሚለው ነው ። እኔም እራስ ወዳድ መሆን አልፈለኩም ። ከኔ ይልቅ ለማራኪክ የበለጠ ስሜት እንዳለህ በትንሹም ቢሆን አውቅ ነበር ። ትናንት ግን ሙሉ በሙሉ አረጋገጥኩኝ ። መልዕክቱንም እኛው ቤት እያለህ ልልክልህ የፈለኩት ፊትህ ላይ ምን አይነት ስሜት እንደሚፈጠር ለማየት ነበር ፤ ደግሞም አየሁት ። አውቃለሁ ምናልባት አንተ ትናንት ስትመጣ ከናንተጋር እሄዳለሁ ልትለን ይሆናል ። እንደዛ የምታደርገው ደግሞ የማራኪክ ፍቅር ሳይወጣልህ ፣ ለኔ ስትል ብቻ እንደሆነ ግልፅ ነው ። ይሄ ደግሞ የኔን ራስ ወዳድነት አጉልቶ ያሳያል ። አንተ በህይወቴ ከመጣህ ጀምሮ እንደ አዲስ መኖር ጀመርኩኝ ፣ ብዙ ነገር አደረክልኝ ። አንተ ያደረክልኝ ነገር ላንተ ምንም መስሎ ሊታይህ ይችላል ። ለኔ ግን ብዙ ነገር ነው ። ብቻዬን ነበርኩኝ ፤ ያውም እስር ቤት ውስጥ ። አንተ ግን መተህ ፈታኸኝ ። ፈተኸኝም ዝም አላልከኝም ፤ አለሜን አሳየኸኝ ። በአንድ ቤት ውስጥ ለአራት ዓመታት ተዘግቶብኝ በፊልም ፣ በመፅሐፍ እና በሙዚቃ የማውቀውን አለም እጄን ይዘህ አሳየኸኝ ። በልቦለድ ላይ የምመኘውን ገፀባህሪ አለበስከኝ ። እናቴ ሰጥታኝ ሰዎች የነጠቁኝን ህይወት መልሰህ ሰጠኸኝ ። ታውቃለህ ፡ ካንተ ጋር ያሳለፍኳት እያንዳንዷ ቅፅበት አሁንም ድረስ ፊቴ ላይ እየተመላለሱ እንደ አዲስ ነፍሴን ወደ ሰማይ ይልኳታል ። ልለይህ መቼም አልፈልግም ነበር ። ይህ ግን ሊሆን አይችልም ። ከዚህ በዋላ እንደ በፊቱ ልጫንህ አልፈልግም ። እኔ ያንተ ብሆንም ፤ አንተ ግን የኔ አይደለህም ። በግድ ደግሞ የኔ ላደርግህ አልሻም ። ምናልባት የፈጣሪ ስራ አይታወቅምና ወደፊት አንድ ቀን አንተን ለኔ ካለ ተመልሰን ልንገናኝ እንችላለን ። ይህ ደግሞ የኔ የወደፊቱ ብቸኛው ምኞቴ ነው ። አሁን ስለኔ ይቅርና ካንተ አንድ የምፈልገው ነገር አለ ። ማራኪህን በጣም ትወዳታለህ ። እሷን እንደ ቀድሞህ ለመመለስ ደግሞ የሚቻልህን ማድረግ አለብህ ። ለፍቅር የሚከፈለውን ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍለህ የራስህ እንድታደርጋት እፈልጋለሁ ። ይሄን ካደረክ ሌላው ሁሉ ትርፍ ነው ። ከዚህ ውጪ ግን ከሶስት ዓመት በዋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሼ እመጣለሁ ። ያኔ ግን ብቻህን ሆነህ ካገኘሁክ የእናቴን ቀን ይስጠኝ አለቅህም ። ድል ባለ ሰርግ አግብቼህ የራሴ አደርግሃለሁ ። እስከዚያው ግን ፈጣሪ መላዕክቶቹን ልኮ ይጠብቅህ ። መልሼ እስካገኝህ በጣም ትናፍቀኛለህ የኔ ጌታ" ይላል መልዕክቱ ። ባለሁበት ደንዝዤ ቀረሁ ። እንደምንም ወደ ራሴ ተመለስኩና ፡ ከዶርም ወጥጬ ወደነ ህይወት ቤት በረርኩኝ ። ቤታቸው በር ላይ ስደርስ ግን ...ያጋጠመኝ ፡ ህይወትን ለማግኘት ተስፋ አስቆራጭ የሆነ ነገር ነው ። ቤታቸው ላይ በትልቁ በፖስተር ተደርጎና በር ላይ ደግሞ ወረቀት ላይ ማስታወቂያ ተፅፎ ተለጥፏል ። "for sell ፡ የሚሸጥ ፣ kan gurguramu" የሚል በሶስት ቋንቋ የተፃፈ ነው ። ከስር ደግሞ ስልክ ቁጥር ተፅፎበታል ። ይሄ ማለት እነ ህይወት ቤቱን ለቀው ወጥተዋል ማለት ነው ። ምናልባት ካሉ ብዬ በሩን በደንብ አንኳኳሁ ፤ ግን ሰሚ የለም ። የህይወት ስልክ ላይ ደወልኩ ፤ ጭራሽኑ አይሰራም ። ተስፋ በቆረጠ አንጀቴ ወደ መጣሁበት ልመለስ አንድ እርምጃ ሳነሳ ከበራቸው ስር የሆነ ፖስታ አየሁኝና ዝቅ ብዬ አነሳሁት ። ገና ስከፍተው የህይወት እንደሆነ በእጅ ፅሁፏ አወኩኝ ። "እዚህ እንደምትመጣ ስላወኩኝ ነው ይሄን ደብዳቤ የፃፍኩልህ ። አየህ አንተ አሁንም ድረስ ሁለት ልብ እንደሆንክ ነው ያለኸው ። ትናንት እንደ ማራኪክ ሆኜ መልዕክት ስልክልህ ወዲያውኑ ፊትህ ተቀያይሮ አባቴ ጋር ጥለኸኝ ሄድክ ። አሁን ደግሞ መልዕክቱ የተላከልህ ከማራኪክ እንዳልሆነ ስትረዳ ወደኔ ሮጠህ መጣህ ። እየወቀስኩህ አይደለም ። እራስህን በደንብ እንድታዳምጥ ስለፈለኩኝ ነው ። አንተ በሁለት ሰዎች መካከል ቆመህ ልብህ እንደ pendulum ወደዛ ወደዚህ እያለብህ ነው ። ይሄ ደግሞ ላንተም ጥሩ አይደለም ። መወሰን አለብህ ፣ መቁረጥ አለብህ ፤ ለዛ ደግሞ ጊዜው አሁን ነው ። ማንንም ጣልቃ ሳታስገባ ከራስህ ጋር የራስህ የሆነ ንግግር አድርግ ። አንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን አንድ መቶ አንድ ጊዜ አስብ ። ሁሉንም መርምር ፤ የሚበጀውን ደግሞ ምረጥ ። ያኔ ያንተ ብቻ ሳይሆን የብዙ ሰው ልብ ያርፋል ። በዚች ምድር ላይ ከአስከፊ በሽታዎች ሁሉ የላቀ ህመም ፤ ቁርጡን ሳያውቁ ዝም ብሎ በተስፋ መቀመጥ ነው ። አገኘው ይሁን ፡ አጣው ይሁን ...? ፣ የኔ ይሁን ወይስ የሌላ እያሉ ቀን ከለሊት ያለ እረፍት ማሰብና መጨነቅ የህመሞች ሁሉ አስከፊው ህመም ነው ። እኔ ደግሞ የዚህ በሽታ ተጠቂ መሆን አልፈልግም ። ወይ አንተን ብቻ ማሰብ ወይም ደግሞ አንተን እስከነ መፈጠርህ መርሳት ይኖርብኛል ። ይሄን ደግሞ ለማድረግ ያንተ እርዳታ ያስፈልገኛል ። አንተ በኔ ላይ ያለህ ተስፋና ለኔ ያለህ ፍቅር ለውሳኔዬ ይረዳኛል ። ለዚሁ መልስ ደግሞ ከመሄዴ በፊት አንድ ዕድል እሰጥህና ለመጨረሻ ጊዜ እንድንገናኝ አደርጋለሁ ። የማገኝህ ያንተን የመጨረሻ ውሳኔ ለማወቅ ብቻ ነው ። ያንቺ ነኝ ወይም ያንቺ አይደለሁም የሚለውን እንድታሳውቀኝ ብቻ ። ይሄን ለማድረግ ደግሞ ግዴታ ቃል ማውጣት አይጠበቅብህም ። ሰኞ #08:00 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ራስ ሆቴል እጠብቅሃለሁ ። በቦታው ላይ በሰዓቱ ከተገኘህ ከኔጋር ለመሆን ፍቃደኛ እንደሆንክ እቆጥረዋለሁ ። ከኔጋር ለመሆን ካልፈለክ ግን ወደ ቦታው መምጣት እራሱ አይጠበቅብህም ። ለብዙ ደቂቃ የምጠብቅህ እንዳይመስልህ ። ባልኩህበት ቦታና ጊዜ በተስፋ እጠብቅሃለው ። እስከዚያው ግን በአካልም ሆነ በስልክ መገናኘት የለብንም ። ከሁሉም ነገር ተገልለህና ብቻህን ሆነህ በንፁህ ህሊናና ልብ በደንብ አስበህበት ላንተም የሚበጀውን ውሳኔ ትወስናለህ ብዬ አስባለሁ ። ስለሁኔታው አባዬ ምንም አያውቅም ። ይሄንን የማደርገው ከሱ ተደብቄ ነው ። ስላንተ ሁሉንም ነገር ነግሬው በጣም ተናዷል ። ፍቅረኛ እንዳለህ ሲሰማ ፊቱ እንዴት እንደተለዋወጠ ብታየው አታውቀውም ። ካሁን በዋላ እንዳገኝህ እንደማይፈልግም ነግሮኛል ። እንደ ምንገናኝ ካወቀ ምን እንደሚያደርግ አላውቅም ። ለማንኛውም እራስህን ጠብቅ ። እስከዚያው ግን ... ። #ህይወት"

@babusem
ይ................
ቀ..................
ጥ...................
ላ....................
ል....................