የኛ ግጥም
45 subscribers
2 photos
2 links
#Kehas

#For business

#gitm

#Tarik

#Feta 😁

#Zena😍

#Sak😀

#desta😇
Download Telegram
💐የከንቲባው ልጅ💐

🔥ክፍል 9


.
.
.
ስትሸና ያው እኔን ማፈሯ አይቀርም ብዬ እንድትከለል ፡ ጫካ እንደሌለ እያወኩ ለወጉ በአይኔ መፈለግ ጀመርኩኝ ። የድሬ ሸገር መንገድ ዳር ላይ መደበቅያ ጫካ ከመፈልግ ፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ዘረኝነትን ማስቆም ይቀላል ። ለነገሩ ሽንት ለመሽናት ጫካው አስፈላጊ አይመስለኝም ። ብዙ ጊዜ መንገድ ስንሄድ ሽንት ሲመጣብን ለዛፎቹ አስበን ይመስል ወደ ጫካ እንሮጣለን ። ከሰው ለመደበቅ ነው እኮ ... ። በነ ጦጢት እየተሾፈን እንደሆነ ማን በነገረን ። anyways ጫካ ስላጣን በመኪናው ተከልላ ሸንታለች ። እኔኮ ግርም የሚለኝ ሰው ሲሸና ጠብቆ ሽንቴ የሚመጣው ጉድ ነው ። ውሃ ስለማልጠጣ ሽንት አዘውትሮ የመሽናት ልምድ የለኝም ። (መሽናቴ ካልቀረ ምን አስጠጣኝ ...) ። #08:00 ሰዓት አልፏል ። አዲስ አበባ ለመግባት በግምት #2 ሰዓት ይቀረናል ። ሸገር ለ #1 ቀን ማደር ስለፈለግን እንጂ ቀጥታ ቢሾፍቱ መሄድ አላቃተንም ። ከስንት ድካም በዋላ ልክ #09:42 ደቂቃ ላይ በአቂቃ ቃሊቲ በኩል አዲስ አበባ ገባን ። መንገዶች ሁሉ በመኪናና ሰዎች ተሸፍኗል ። እንደምንም ክፍት መንገድ ባየን ቁጥር እየሾለክን ቦሌ ካንዱ ሆቴል ጎራ ብለን #1 ክፍል ያዝን ። በጣም ደክሞን ስለነበር ሁለታችንም ሻዎር ገባን (አንድላይ አይደለም ፡ ብቻ ለብቻ ነው ደግሞ...) ። እንግዲህ ዛሬን ሸገር ላይ ፍልስስ ልንል ነው ። አዲስ አበባ እንደ ድሬ አይደለችም ። የሰው ብዛት ፣ የመኪናው ጋጋታ ፣ የህንፃዎቹ ብዛትና ውበት ፣ የከተማው ስፋት ፣ ባጠቃላይ ሸገር እንደ ድሬ ቶሎ ምትለመድ አይነት አይደለችም ። እዛው ከያዝነው ሆቴል እራት በልተን ፡ ወይን እየጠጣን ስሟን ለመምሰል ሌት ተቀን ደፋ ቀና የምትለዋን ከተማ ከላይኛው ፎቅ ቁልቁል ወደታች እያየናት ነው ። ሆቴሉ ግሩም ነው ፤ ከላይ በሁሉም አቅጣጫ ከተማዋን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል ። ምሽት ላይ ከላይ ስትታይ ስሟን ትመሰላለች ። የከንቲባው ልጅ "ወይ አዲስ አበባ" እያለች ትገረማለች ። ከዛን ወደኔ ዙራ "ስማኝማ ፡ ፈታ ልንል ነው አይደል ይሄን ሁሉ ርቀት አቋርጠን የመጣነው ...?" አለችኝ ። አዎ ስላት "እንደዛ ከሆነ ፡ በናትህ ፡ ስወድህ ፡ night club ውሰደኝ" አለችኝ ። "ጀማሪ እረኛ ፡ ከብት አያስተኛ" ይለዋል የሀገሬ ሰው ። ልጅቷ እቤት ሆና በፊልም ያየችውን ነገር ባካል ማየትና ማድረግ ትፈልጋለች ። ደግነቱ ከያዝነው ሆቴል አጠገብ club ይታየኛል ። እጅ ለእጅ ተያይዘን ወደዛው አመራን ። entrance / መግቢያ ከፍለን ፡ ተፈትሸን ገባን ። ጎበዝ ፡ ወጣቱ እዚህ አ እንዴ ያለው ። ለካ ኢትዮጵያ ወደ ዋላ የቀረችው ወዳ አይደለም ። መደማመጥ የለም ፡ ጭፈራ ብቻ ነው ። የእስፒከሩ ጩኸት ፣ የሰው ጫጫታና ዳንስ ቦታውን ሶሪያ አስመስሎታል ። "እንቅስቃሴዎች ሁሉ dance ናቸው" የሚለውን ዘፈን teddy yo እዚህ ቤት ቁጭ ብሎ የፃፈ ይመስላል ። እኔ እንኳን club ስገባ የመጀመሪያዬ ስለሆነ ስራቴን ይዤ ቁጭ ብያለሁ ። ባይሆን መጠጧን አንድ ሁለት እያልኩኝ ፡ ትርዒቱን እያየሁ ልምድ እየቀሰምኩ ነው ። ልጅት ደግሞ በስሜት አሸሸ ገዳሜውን ለመቀላቀል #1mm ነው የቀራት።

"ሂድልኝ ሀዘን ጭንቀቴ ፡ ደስታዬ ና ወደኔ ፣
ጥፋልኝ ሀዘን ህመሜ ፡ ደስታዬ ና ወደኔ" ።
ብቻችሁን መምጣት ክልክል ነው የተባለ ይመስል ፡ ሁሉም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የመጡት (ልክ እንደኛው ...) ። የፈራሁት አልቀረም ፡ የከንቲባው ልጅ እጄን ይዛ አስነስታኝ ትርዒቱ መሃል ቁጭ (ይቅርታ ቁም ለማለት ነው ...) ። እንቅስቃሴ ጀምረናል ፡ ለነገሩ dance ላይ ብዙም የስራ ልምድ ስለሌለኝ እየጨፈርኩ ሳይሆን እየተወላገድኩ ነው ብል ይቀለኛል ። በመሀል በመሀል አንድ ሁለቱን ፡ ሶስት አራት እያልነው ነው ። ፊልም ላይ አረቄ /Jin ባንድ ትንፋሽ እንደዛ ሲጨልጡት በውሃ የሚያታልሉን ይመስለኝ ነበር ። ዛሬ ግን በአይኔ በብረቱ አይቼ አምኛለሁ (አይን ብረት ነው እንዴ ...) ። ኧረ ሴቶቻችን ተበላሽተዋል ጎበዝ ። ከወንዶቹ ይልቅ እነሱ ባሱኮ ። የሌሎቹ ሲገርመኝ የኔዋ ጉድ ብሳ ተገኘች ። እየጠጣን ፣ እየጨፈርን ፣ እያረፍን ፣ በድጋሚ የአሁኑን step እየደገምን በስተመጨረሻ ልጅቷ ውሃ ሆና እላዬ ላይ ተዘረገፈች ። እንዴት ተሸክሜያት ከክለቡ እስከ ያዝንበት ሆቴል እንዳደረስኳት ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው (እኔም ግን አውቃለሁ ...) ። በስንት ድካም የያዝነው ክፍል ደረስንና አልጋው ላይ ዘረገፍኳት ። ንሰሐ ገብቼ ሀጥያቴን የተናዘዝኩ ያክል ነው ቅልል ያለኝ ። የለበሰችው አጭር ቀሚስ ገላዋን ሙሉ በሙሉ የመሸፈን አቅም አልነበረውም ። በቀላል maths ከወገብ በታች አካሏ #80% ይታያል ። አልተን ገዳገድኩም እንጂ መጠጡ አናቴ ላይ ወጥቷል ። እሷ ግን የት እንዳለች እራሱ የምታውቅ አይመስለኝም ። የያዝነው #1 ክፍል ቢሆንም #2 አልጋ አለው ። እኔ አልጋዬ ላይ ሆኜ በእውን እያየዃት ፤ እሷ ደግሞ በስካር አለም ተወስዳ ተኝታለች ። የሰው ልጅ ከእንስሳ የሚለየው እራሱን መግዛት በመቻሉ ነው ። እንስሳት እራሳቸውን መግዛት ስለማይችሉ ያገኙትን በልተው ፣ ካገኙት ጋር ወስበው ፣ ሂድ ወደ ተባሉበት ሄደው ይኖራሉ እንጂ እንደ ሰው በእቅድና አላማ አይንቀሳቀሱም ። የሰው አፈጣጠር ግን ይለያል ። ህሊና ከሚባል ዳኛ ጋር ስለተፈጠረ በጎ ሲያደርግ በርታ ፣ መጥፎውን ነገር ሊሰራ ሲል ደግሞ እረፍ ፣ ከሰራም በዋላ ደግሞ በድለሀል ይቅር በል የሚል ከሳሽ አይምሮው ውስጥ ተቀምጧል ። የሰው ልጅ በሁለት መንገድ ይበድላል ። አውቆና ሳያውቅ ። ሳያውቁ ያደረጉት ይሁን ፤ ነገር ግን እያወቁ ማጥፋት የጥፋት ሁሉ ጥፋት ነው ። ብዙ ጊዜ ስካርን ተገን በማድረግ ብዙ ስተት ይፈፀማል ። በዚች ሰዓት እኔ እራሴን አልሳትኩም ። ስለዚህ እራሴን መግዛት እችላለሁ ማለት ነው ። መጥፎ ነገርን አለማድረግ እየተቻለ ማድረግ ሰይጣንነት ነው ። ይቺ ልጅ እዚህ ድረስ አብራኝ የመጣችው ስላመነችኝ ነው ። በዚህ ዘመን ደግሞ የሰውን እምነት ማግኘት የማይገኝ ትልቁ ፀጋ ነው ። ወደሷ ጠጋ ብዬ ጫማዋን አወለኩላት ። ወደ ከንፈሯ ተጠጋሁና ጆሮዬን አፏ ላይ ደቀንኩት ። ትንፋሿ ሰውነቴን ውርር ስያደርገኝ በህይወት እንዳለች አረጋገጥኩኝ ። አይኖቼ ከእግር እስከ እራስ ፀጉሯ ድረስ scan አረጓት ። ይሄ ነገር ወንድነቴን እየተፈታተነው ነው መሰለኝ ።


ይ................
ቀ..................
ጥ...................
ላ....................
ል....................