🚨 #አዲሱ_የካሳ_ህግ_ማብራሪያ ⁉️⤵️
አዲሱ የካሳ አዋጅ ቁጥር 1161/2012 አንቀጽ 2(2) የንብረት ካሳ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት ወይም ላደረገው ቋሚ ማሻሻያ በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል።
#ቋሚ ማሻሻያ ማለት በይዞታው ላይ የሚሰራ የምንጣሮ፣ ድልደላ እርከን ስራ፣ ውሃ የመከተር ስራ እና የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉት ስራዎች ይጠቃለላል በማለት ይደነግጋል ፡፡ በመሆኑም አዲሱ አዋጅ የተሻለ ነገር ይዞ የመጣው ካሳ የሚከፈለው ለሰፈረ ንብረት እና ለተደረገ ቋሚ ማሻሻል እንደሆነ ይደነግጋል፡፡
#ቋሚ ማሻሻል የሚለው አሁንም ሌላ ውዝግብ የሚያስነሳ ነው ምክንያቱም ከተዘረዘሩት ድርጊቶች ውጪ ያደረገው ለምሳሌ መሬት በተለያየ መንገድ ለም እንዲሆን፣ ምርታማ እንዲሆን የሰራው ስራ በየትኛው ነው ሚካተተው? ምንጣሮ ነው?
#አዲሱ_ አዋጅ_የያዛቸው_ትሩፋቶች
(1) #የቀዳሚነት መብት፡-
ቀድሞ በነበረው አዋጅ 455/97 ያልነበረ ነገር ግን አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አካቶ ያወጣው ሰዎች ቀድሞ ለፍተው ባለሙት የመሬት ይዞታቸው አቅም ያላቸው በሆኑ ጊዜ በከተማ ፕላን መሰረት ለብቻቸው ወይም በጣምራ ማልማት የሚችሉበት የቀዳሚነት መብት በአንቀጽ 7 ስር ማጎናፀፋ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(2) #ካሳ የማግኘት መብት:-
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አንቀፅ 8(1)(ሰ) ስር የልማት ተነሺውን ማስነሳት የሚቻለው ለተነሺው ካሳ ከተፈለ እና ምትክ ቦታ ወይም ቤት ከሰጠ በኋላ መሆን እንዳለበት አዋጁ ይደነግጋል፡፡በመሆኑም ሰዎች በይዞታቸው ካሳም ሳይከፈላቸው ምትክ ቦታም ሳይሰጣቸው እንዲነሱ ተደርጎ የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው የነበሩ ባለይዞታዎች በጣም ብዙ የነበሩ በመሆኑ ይህ አዋጅ ህዝቡ ውስጥ የነበረው ችግር ለመፍታት ተነሺዎች ከመነሳታቸው በፊት አስቀድመው ካሳ እና ምትክ ቦታ ማግኘት እንዳለባቸው መደንገጉ በሕግ ደረጃም ቢሆን ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(3) #ካሳ በወቅቱ ካልተከፈላቸው መልሶ የመያዝ መብት
ተነሺዎች የካሳ ግምት በጹሑፍ እንዲያውቁ ከተደረገ ቀን ጀምሮ በሶስት ወር ውስጥ ካሳ ካልተከፈላቸው በመሬት ይዞታቸው ከቋሚ ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሳ ካልተከፈው በፕላን የሚፈቀድ እና ቀጣይ የቦታውን የልማት ወጪ በመንግስት ላይ የማያበዛ በመሬቱ ላይ ማንኛውም ስራ መስራት ይችላል በማለት ይደነግጋል።
ቢሆንም ግን ይህ ድንጋጌ እጅግ አሻሚ ነው ምክንያቱም መንግስት ካሳ ካልከፈለ በፕላን መሰረት ባለይዞታ ማንኛውንም ዓይነት ስራ መስራት እንደሚችል ከተደነገገ በኋላ በመንግስት የልማት ወጪ የማያበዛ ስራ ማለቱ ምን ማለት ነው? እጅግ በጣም ግልጽ ነት የጎደለው ነው፡፡
(4) #ተመጣጣኝ ካሳ ክፍያና ምትክ ቦታ
አዲሱ አዋጅ በመሬቱ ላይ ለተፈራ ንብረት፣ ቋሚ ማሻሻያ ባለይዞታው ንብረቱን ማዘዋወር የሚችል ከሆነ የማዘዋወሪያ ወጪ ወይም የትራንስፖርት/የማጓጓዣ ወጪ ከመክፈሉ በተጨማሪ ከገጠር መሬት ይዞታ ለሚነሳ የመሬት በላይዞታ ተነሺ ከተወሰደበት መሬት ተመጣጣኝ የሆነ ምትክ መሬት እና መሬት ይዞታው ከመልቀቅ በፊት ባሉ ሶስት ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ምርት ያመረተበትን ምርት በወቅታዊ ዋጋ ተሰልቶ በ15 ተባዝቶ ይከፈላል በማለት ይደነግጋል፡፡
(5) #በአዋጅ አንቀጽ 2(4) የልማት ተነሽ ድጋፍ የመሬት ባለይዞታ ከመሬቱ በጊዜያዊም ሆነ በቋሚነት ሲነሳ ከአዲሱ አከባቢ ጋር መላመድ እንዲችል ከንብረት እና ከልማት ተነሽ ካሳ በተጨማሪ በዓይነት ወይም በገንዘብ የሚሰጥ ድጋፍ ነው፡፡ it is promising move አዲስ እና በጣም ጥሩ የሚባል ነው ነገር ግን ይህ ነገር የሚወሰነው በክልሎች መመሪያ ነው፣ መች ይሁን የሚወጣው? ባይወጣስ?
(6) #የወል ይዞታዎች ላይ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
በእርግጥ ወል ይዞታና የመንግስት የወል የተቀላቀለ በመሆኑ በወል ይዞታዎች ላይ ካሳ ሲከፈል አይታይም፣ በዚህ አዋጅ የወል ይዞታ ማለት ከመንግስት ወይም ከግል ይዞታነት ውጭ የሚገኝና የአከባቢው ማህበረሰብ ለግጦሽ፣ ለደንና ለማህበራዊ አገልግሎት በጋራ የሚጠቀሙበት የመሬት ይዞታ ነው በማለት አንቀፅ 2(11) ይደነግጋል።
በመሆኑ የወል ይዞታዎች አገኘን ተብሎ በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካል መሸንሸን አይችሉም ማለት ነው፡፡ የወል መሬቱ የካሳ ስሌት የወል መሬቱ ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወይም ጥቅሙ የቀረባቸውን የአኗኗር ዘይቤ ወይም መተዳደሪያ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ማለት ነው? አሁንም ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡የወል መሬቱ የተወሰደባቸው የወል መሬቱ ተጠቃሚ አካል የተገኘው ገንዘብ ለማህበረሰቡ አባላት እኩል ሊካፈል ወይም በዓይነት ሊጠቀሙበት የሚችሉበትን መንገድ መቅረጽ አለበት በማለት አንቀፅ 13(3) ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የወል መሬት ያለካሳ የሚወስድ የመንግስት አካል ከድርጊቱ መቆጠብ አለበት፡፡
(7) #የልማት ተነሺ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
የከተማ መሬት ባለይዞታ ከይዞታው በቋሚነት ተነሽ በሚሆንበት ጊዜ የሚከፈለው የልማት ተነሺ ካሳ እና የሚሰጠው ምትክ ቦታ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡
የልማት ተነሺ ካሳ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡ይህ አይነቱ ካሳ የመጠቀም መብት በመኖሩ ብቻ የሚገኝ የካሳ ዓይነት ነው፡፡ ለከተማ ተነሺ በአከባቢ ለነበረው የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና ለሚደርሰው የስነ-ልቦና ጉዳት ማካካሻ ይከፈለዋል መጠኑ በደንብ ይወሰናል 13(4)(ሠ) በማለት ይደነግጋል፡፡
ግን ይህ ካሳ በተግባር ተከፍሎ አያውቅም። #የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስ-ልቦና ጉዳት ካሳ ማለት ለተጎጂ ከነበረበት አከባቢ በመነሳቱ የነበረው ማህበራዊ ትስስር በመቋረጡ የሚከፈል የጉዳት ማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
በመሆኑም በከተማ መሬት ይዞታ የሚነሳ ሰው የልማት ተነሺነት ካሳ፣ምትክ ቦታ፣ቤት ፈርሶበት ከሆነ የቤት መስሪያ ዋጋና በቦታው እስኪገባ ባለው 2 ዓመት የሚኖርበት ቤት ወይም የወቅታዊ የኪራይ ገንዘብ ግምት እና የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስነ-ልቦና ጉዳት ካሳ ይከፍለዋል፡፡በመሆኑም እነዚህ መብቶች በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ ጥሩና ተስፋ ሰጪ የመሬት ካሳ መብቶች ናቸው፡፡
#መልሶ ማቋቋም ፡- በአዋጅ አንቀጽ 16 የክልል መንግስት ወይም የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ አስተዳደር ለካሳ ክፍያ እና ለመልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቋቁማል በማለት ይደነግጋል፡፡ መልሶ ማቋቋም ማለት በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ የሚያስችል የሚሰጥ ድጋፍ ነው ። ጥያቄው ግን መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ባይቋቋምስ ❓ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሰት እርከን ካሳን በሚመለከት አቤቱታ የሚሰማ ኮሚቴ አንኳን አላቋቋሙም መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቁማሉ ❓
አዲሱ የካሳ አዋጅ ቁጥር 1161/2012 አንቀጽ 2(2) የንብረት ካሳ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት ወይም ላደረገው ቋሚ ማሻሻያ በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል።
#ቋሚ ማሻሻያ ማለት በይዞታው ላይ የሚሰራ የምንጣሮ፣ ድልደላ እርከን ስራ፣ ውሃ የመከተር ስራ እና የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉት ስራዎች ይጠቃለላል በማለት ይደነግጋል ፡፡ በመሆኑም አዲሱ አዋጅ የተሻለ ነገር ይዞ የመጣው ካሳ የሚከፈለው ለሰፈረ ንብረት እና ለተደረገ ቋሚ ማሻሻል እንደሆነ ይደነግጋል፡፡
#ቋሚ ማሻሻል የሚለው አሁንም ሌላ ውዝግብ የሚያስነሳ ነው ምክንያቱም ከተዘረዘሩት ድርጊቶች ውጪ ያደረገው ለምሳሌ መሬት በተለያየ መንገድ ለም እንዲሆን፣ ምርታማ እንዲሆን የሰራው ስራ በየትኛው ነው ሚካተተው? ምንጣሮ ነው?
#አዲሱ_ አዋጅ_የያዛቸው_ትሩፋቶች
(1) #የቀዳሚነት መብት፡-
ቀድሞ በነበረው አዋጅ 455/97 ያልነበረ ነገር ግን አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አካቶ ያወጣው ሰዎች ቀድሞ ለፍተው ባለሙት የመሬት ይዞታቸው አቅም ያላቸው በሆኑ ጊዜ በከተማ ፕላን መሰረት ለብቻቸው ወይም በጣምራ ማልማት የሚችሉበት የቀዳሚነት መብት በአንቀጽ 7 ስር ማጎናፀፋ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(2) #ካሳ የማግኘት መብት:-
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አንቀፅ 8(1)(ሰ) ስር የልማት ተነሺውን ማስነሳት የሚቻለው ለተነሺው ካሳ ከተፈለ እና ምትክ ቦታ ወይም ቤት ከሰጠ በኋላ መሆን እንዳለበት አዋጁ ይደነግጋል፡፡በመሆኑም ሰዎች በይዞታቸው ካሳም ሳይከፈላቸው ምትክ ቦታም ሳይሰጣቸው እንዲነሱ ተደርጎ የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው የነበሩ ባለይዞታዎች በጣም ብዙ የነበሩ በመሆኑ ይህ አዋጅ ህዝቡ ውስጥ የነበረው ችግር ለመፍታት ተነሺዎች ከመነሳታቸው በፊት አስቀድመው ካሳ እና ምትክ ቦታ ማግኘት እንዳለባቸው መደንገጉ በሕግ ደረጃም ቢሆን ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(3) #ካሳ በወቅቱ ካልተከፈላቸው መልሶ የመያዝ መብት
ተነሺዎች የካሳ ግምት በጹሑፍ እንዲያውቁ ከተደረገ ቀን ጀምሮ በሶስት ወር ውስጥ ካሳ ካልተከፈላቸው በመሬት ይዞታቸው ከቋሚ ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሳ ካልተከፈው በፕላን የሚፈቀድ እና ቀጣይ የቦታውን የልማት ወጪ በመንግስት ላይ የማያበዛ በመሬቱ ላይ ማንኛውም ስራ መስራት ይችላል በማለት ይደነግጋል።
ቢሆንም ግን ይህ ድንጋጌ እጅግ አሻሚ ነው ምክንያቱም መንግስት ካሳ ካልከፈለ በፕላን መሰረት ባለይዞታ ማንኛውንም ዓይነት ስራ መስራት እንደሚችል ከተደነገገ በኋላ በመንግስት የልማት ወጪ የማያበዛ ስራ ማለቱ ምን ማለት ነው? እጅግ በጣም ግልጽ ነት የጎደለው ነው፡፡
(4) #ተመጣጣኝ ካሳ ክፍያና ምትክ ቦታ
አዲሱ አዋጅ በመሬቱ ላይ ለተፈራ ንብረት፣ ቋሚ ማሻሻያ ባለይዞታው ንብረቱን ማዘዋወር የሚችል ከሆነ የማዘዋወሪያ ወጪ ወይም የትራንስፖርት/የማጓጓዣ ወጪ ከመክፈሉ በተጨማሪ ከገጠር መሬት ይዞታ ለሚነሳ የመሬት በላይዞታ ተነሺ ከተወሰደበት መሬት ተመጣጣኝ የሆነ ምትክ መሬት እና መሬት ይዞታው ከመልቀቅ በፊት ባሉ ሶስት ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ምርት ያመረተበትን ምርት በወቅታዊ ዋጋ ተሰልቶ በ15 ተባዝቶ ይከፈላል በማለት ይደነግጋል፡፡
(5) #በአዋጅ አንቀጽ 2(4) የልማት ተነሽ ድጋፍ የመሬት ባለይዞታ ከመሬቱ በጊዜያዊም ሆነ በቋሚነት ሲነሳ ከአዲሱ አከባቢ ጋር መላመድ እንዲችል ከንብረት እና ከልማት ተነሽ ካሳ በተጨማሪ በዓይነት ወይም በገንዘብ የሚሰጥ ድጋፍ ነው፡፡ it is promising move አዲስ እና በጣም ጥሩ የሚባል ነው ነገር ግን ይህ ነገር የሚወሰነው በክልሎች መመሪያ ነው፣ መች ይሁን የሚወጣው? ባይወጣስ?
(6) #የወል ይዞታዎች ላይ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
በእርግጥ ወል ይዞታና የመንግስት የወል የተቀላቀለ በመሆኑ በወል ይዞታዎች ላይ ካሳ ሲከፈል አይታይም፣ በዚህ አዋጅ የወል ይዞታ ማለት ከመንግስት ወይም ከግል ይዞታነት ውጭ የሚገኝና የአከባቢው ማህበረሰብ ለግጦሽ፣ ለደንና ለማህበራዊ አገልግሎት በጋራ የሚጠቀሙበት የመሬት ይዞታ ነው በማለት አንቀፅ 2(11) ይደነግጋል።
በመሆኑ የወል ይዞታዎች አገኘን ተብሎ በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካል መሸንሸን አይችሉም ማለት ነው፡፡ የወል መሬቱ የካሳ ስሌት የወል መሬቱ ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወይም ጥቅሙ የቀረባቸውን የአኗኗር ዘይቤ ወይም መተዳደሪያ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ማለት ነው? አሁንም ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡የወል መሬቱ የተወሰደባቸው የወል መሬቱ ተጠቃሚ አካል የተገኘው ገንዘብ ለማህበረሰቡ አባላት እኩል ሊካፈል ወይም በዓይነት ሊጠቀሙበት የሚችሉበትን መንገድ መቅረጽ አለበት በማለት አንቀፅ 13(3) ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የወል መሬት ያለካሳ የሚወስድ የመንግስት አካል ከድርጊቱ መቆጠብ አለበት፡፡
(7) #የልማት ተነሺ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
የከተማ መሬት ባለይዞታ ከይዞታው በቋሚነት ተነሽ በሚሆንበት ጊዜ የሚከፈለው የልማት ተነሺ ካሳ እና የሚሰጠው ምትክ ቦታ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡
የልማት ተነሺ ካሳ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡ይህ አይነቱ ካሳ የመጠቀም መብት በመኖሩ ብቻ የሚገኝ የካሳ ዓይነት ነው፡፡ ለከተማ ተነሺ በአከባቢ ለነበረው የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና ለሚደርሰው የስነ-ልቦና ጉዳት ማካካሻ ይከፈለዋል መጠኑ በደንብ ይወሰናል 13(4)(ሠ) በማለት ይደነግጋል፡፡
ግን ይህ ካሳ በተግባር ተከፍሎ አያውቅም። #የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስ-ልቦና ጉዳት ካሳ ማለት ለተጎጂ ከነበረበት አከባቢ በመነሳቱ የነበረው ማህበራዊ ትስስር በመቋረጡ የሚከፈል የጉዳት ማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
በመሆኑም በከተማ መሬት ይዞታ የሚነሳ ሰው የልማት ተነሺነት ካሳ፣ምትክ ቦታ፣ቤት ፈርሶበት ከሆነ የቤት መስሪያ ዋጋና በቦታው እስኪገባ ባለው 2 ዓመት የሚኖርበት ቤት ወይም የወቅታዊ የኪራይ ገንዘብ ግምት እና የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስነ-ልቦና ጉዳት ካሳ ይከፍለዋል፡፡በመሆኑም እነዚህ መብቶች በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ ጥሩና ተስፋ ሰጪ የመሬት ካሳ መብቶች ናቸው፡፡
#መልሶ ማቋቋም ፡- በአዋጅ አንቀጽ 16 የክልል መንግስት ወይም የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ አስተዳደር ለካሳ ክፍያ እና ለመልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቋቁማል በማለት ይደነግጋል፡፡ መልሶ ማቋቋም ማለት በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ የሚያስችል የሚሰጥ ድጋፍ ነው ። ጥያቄው ግን መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ባይቋቋምስ ❓ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሰት እርከን ካሳን በሚመለከት አቤቱታ የሚሰማ ኮሚቴ አንኳን አላቋቋሙም መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቁማሉ ❓
https://ermitheethiopia.com/listing/condominium-for-sale-in-addis-ababa-code-jb-349/?doing_wp_cron=1630945728.2402210235595703125000
Condominium for sale in addis ababa code-JB- 349
Condominium for sale in addis ababa code-JB- 349
https://ermitheethiopia.com/listing/g1-residential-building-for-rent-code-ap-350/?doing_wp_cron=1630946865.4354000091552734375000
G+1 Residential building for Rent code-AP- 350
G+1 Residential building for Rent code-AP- 350
https://ermitheethiopia.com/listing/toyota-hilux-for-sale-in-addis-ababa-code-ab-351/
Toyota hilux for sale in addis Ababa code- AB-351
Toyota hilux for sale in addis Ababa code- AB-351
https://ermitheethiopia.com/listing/new-villa-house-for-sale-in-addis-ababa-code-yk-348/?doing_wp_cron=1630949110.4426400661468505859375
New villa house for sale in addis ababa code-YK- 348
New villa house for sale in addis ababa code-YK- 348
https://ermitheethiopia.com/listing/brand-new-apartment-for-rent-around-bole-code-ap-352/?doing_wp_cron=1631031159.5012769699096679687500
Brand new apartment for rent around bole code-AP-352
Brand new apartment for rent around bole code-AP-352
https://ermitheethiopia.com/listing/apartments-guest-house-for-rent-around-kazanchis-code-ap-353/?doing_wp_cron=1631033353.4657111167907714843750
Apartments Guest house for rent around Kazanchis code-AP-353
Apartments Guest house for rent around Kazanchis code-AP-353
https://ermitheethiopia.com/listing/hoyundia-atoz-for-sale-in-addis-ababa-code-al-354/?doing_wp_cron=1631101023.4888949394226074218750
Hoyundia atoz for sale in addis ababa code -AL- 354
Hoyundia atoz for sale in addis ababa code -AL- 354
https://ermitheethiopia.com/listing/toyota-hilux-double-cab-for-sale-in-addis-ababa-code-jb-355/?doing_wp_cron=1631102663.5048739910125732421875
Toyota hilux double cab for sale in addis ababa code-JB- 355
Toyota hilux double cab for sale in addis ababa code-JB- 355
https://ermitheethiopia.com/listing/suzuki-every-for-sale-in-addis-ababa-code-al-356/?doing_wp_cron=1631115569.0415999889373779296875
Suzuki Every for sale in addis ababa code -AL- 356
Suzuki Every for sale in addis ababa code -AL- 356
https://ermitheethiopia.com/listing/new-villa-house-for-sale-code-jb-357/?doing_wp_cron=1631124959.7277851104736328125000
New villa house for sale code-JB- 357
New villa house for sale code-JB- 357
https://ermitheethiopia.com/listing/apartments-guest-house-around-bole-code-ap-343/?doing_wp_cron=1631125276.6514079570770263671875
Apartments Guest house around bole code-AP- 344
Apartments Guest house around bole code-AP- 344
❗#የንብረት መብት : የመሬት ይዞታ መብት እና የቤት ባለቤትነት መብት
#የንብርት መብት
ማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ የግል ንብረት የማፍራት መብት እንዳለው፣ ይህ መብትም ንብረትን የመያዝ፣ በንብረቱ የመጠቀም፣ ንብረቱን በስጦታ፣ በውርስ ወይም በሽያጭ ወይም በሌላ ማኛውም መንገድ የማስተላለፍ መብቶችን የሚያጎናጽፍ ሰፊ መብት ሲሆን በህግም ጥበቃ የሚደረግለት መብት ነው፡፡
ይሁን እንጅ ይህ በህግ ጥበቃ የሚደረግለት ንብረት የማፍራት መብት የአብዛኛውን ህዝብ መብት ወይም ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል በህግ ሊገደብ አንደሚችል ከህገመንግስቱ አንቀጽ 40 በግልጽ መረዳት ይቻላል፡፡ የግል ንብረት ባለቤትነት መብት የሚመነጨው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ወይም ህጋው ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች በጉልበታቸው፣ በመፍጠር ችሎታቸው ወይም በካፒታላቸው ያፈሩት ሲሆን የንብረት መብት ይኖራቸዋል፡፡ ንበረት ግዙፍነት ያለው ሁኖ የሚንቀሳቀስና፣ የማይንቀሳቀስ ተብሎ ሊከፈል ይችላል(የፍ/ህ/ቁ 1127)፡፡
የመሬት ይዞታ መብት እና የቤት ባለቤትነት የንብረት መብቶች ግዙፍነት ያላቸው የንብረት መብቶች ሲሆኑ ከማይነቀሳቀሱ የንብረት መብቶች ውስጥ የሚመደቡ ናቸው (የፍ/ህ/ቁ 1030)፡፡ ይህም ሁለቱን መብቶች አንድ የሚያደርጋቸው የመጀመርያው ጉዳይ ነው፡፡
የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት ባለቤት መንግስት እና ህዘብ ብቻ እንደሆነ እና መሬትን መሸጥ በህግ የተከለከለ ስለመሆኑ በህገመንግስቱ ተደነግጓል፡፡ ዜጎች በመሬት ላይ ያላቸው መብት የመሬት ይዞታ መብት ሲሆን ከሽያጭ በስተቀር በመሬቱ ላይ የመጠቀም፣ የይዞታ መብታቸውን በስጦታ፣ በውርስና በኪራይ ለማስተላለፍ ይችላሉ፡፡ ይህ የመሬት ይዞታ መብትም እንደማንኛውም ግዙፍነት ያለው የንብረት መብት በህግ ጥበቃ የሚደረግለት ሰፊ መብት ነው፡፡
በሌላ በኩል የግል የቤት ባለቤትነት መብት ደግሞ ለሁሉም ዜጎች እና ህጋዊ ሰውነት ላላቸው ድርጅቶች በእኩልነት የተሰጠ መብት ሲሆን የቤት በለንብረት የሆነ ግለሰቦች ወይም ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች በቤቱ ላይ የመጠቀም፣ በስጦታ ወይም በውርስ የማስተላለፍ፣ የመሸጥ እና በሌላ ማንኛውም መንገድ ንብረቱን ለሌላ ወገን የማስተላለፍ መብት የሚሰጥ ነው፡፡
የመሬት ይዞታ መብት እና የቤት ባለቤትነት መብቶች መካከል ምን አይነት ግንኙነት ሊኖር ይችላል?
ቤት የሚገነባው በመሬት ላይ ነው፡፡ መሬት ደግሞ የመንግስት እና የህዝብ ነው፡፡ መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ የተገነባ ቤት እንዴት ዜጎችን የግል የንብረት መብት ሊያጎናጽፋቸው ይችላል የሚሉት ነጥቦች በዚህ ጽሁፍ ውስጥ የሚዳሰሱ ነጥቦች በመሆናቸው እንደሚከተለው ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡
#በመሬት ይዞታ መብት እና በቤት ባለቤትነት መብቶች መካከል ምን አይነት ግንኙነት ሊኖር ይችላል?
የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እና ዘላኖች መሬትን ለግጦሽም ሆነ ለእርሻ በነጻ የማግኘት እና ከርስታቸው ያለመነቀል ወይም ያለመፈናቀል መብት እናዳለቸው እንዲሁም የግል ባለሃብቶች በህግ በሚወሰን ክፍያ ከመንግስት መሬት ማግኘት እንደሚችሉ በህገመንግስቱ ተደንግጓል (አንቀጽ 40(4፣5፣6))፡፡ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እና ዘላኖች መሬትን በነጻ ከመንግስት የሚያገኙ ስሆን ሌላው ዘጋ ወይም ህዝብ ግን የመሬት ይዞታ መብቱን የሚያገኘው በክፍያ ነው፡፡ ይህ የህገመንግስቱ ክፍል ከአርሶአደሮች እና ዘላኖች በስተቀር ያሉትን ዜጎች በሃገሪቱ ማንኛውም የኢኮነሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የመሳተፍን እና በሃገሪቱ ሃብት እኩል የመጠቀም እና በእኩልነት የመልማት ህገመንግስታዊ መባታቸውን የሚገድብ መሆኑን ማስተዋል ይቻላል፡፡
ሆኖም ግን የመሬት ይዞታ መብት በነጻ ወይም በህግ በሚወሰን ክፍያ ከመንግስት የሚገኝ ሲሆን የቤት ባለቤትነት መብት ግን በግዥ፣ በስጦታ፣ በውርስ፣ ወይም በሌላ መንኛውም መንገድ የሚገኘ ሊሆን ይችላል፡፡ እዚህ ላይ ሊተኮርበት የሚገባው ጉዳይ ቤቱ የተገነባው መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ መሆኑ እና የተገነባውን ቤት ከመሬቱ ተነጥሎ ሊታይ የሚችል ንብረት አለመሆኑ ነው፡፡ ግንባታው ከመሬቱ ተነጥሎ ሊታይ የሚችል ካልሆነ ደግሞ የመሬት ይዞታ መብትን በህግ በተወሰነ ክፍያ ከመንግስት ተረክቦ ቤት የገነባ የቤት ባለቤት ባለቤት ያልሆነበትን መሬት ወይም በመሬቱ ጨምሮ በሽያጭ ማስተላለፍ እንደሚችል ለመገንዘብ የሚከብድ ጉዳይ አይደለም፡፡ ስለሆነም የመሬት ይዞታ መብትን እና የቤት ባለቤትነትን አንድ የሚያደርጋቸው ሁለተኛው ምክንያት የመሬት ይዞታ መብት ቤት ከተገነባበት በኋላ በሽያጭ ለሌላ ወገን ሊተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ እዚህ ላይ መሬትን በሽያጭ ማስተላለፍ እና የመሬት ይዞታ መብትን በሽያጭ ማስተላለፍ ግን ተመሳሳይ ትርጉም ሊሰጣቸው እንደማይችል ልብ ሊሉ ይገባል፡፡
መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ የተገነባ ቤት እንዴት ዜጎችን የግል የንብረት መብት ሊያጎናጽፋቸው ይችላል?
ከፍ ሲል እንደገለጽሁት መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ የመንግስት እና የኢትዮጵያ ህዝቦች ንብረት ነው፡፡ ይህም ማለት መንግስት ከሽያጭ በስተቀር መሬትን በሌላ ማንኛውም መንገድ ማስተላለፍ የሚችል ስለመሆኑ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ስለሆነም ዜጎች መሬትን ከመንግስት በነጻ ወይም በክፍያ የሚያገኙት ቢሆነም በዚሁ መሬት ላይ ያላቸው መብት ግን የመሬት ይዞታ መብት ብቻ ነው፡፡ ይህም ማለት ማንኛውም የመሬት ይዞታ መብት ያለው (Possessor) ሁሉ መሬቱን ከመሸጥ በስተቀር መሬቱን የመያዝ፣ በመሬቱ የመጠቀም፣ መሬቱን በስጦታ፣ በውርስ ወይም በኪራይ የማስተላለፍ መብቶች ሁሉ የሚያጠቃልል ነው፡፡
አንድ የመሬት ይዞታ መብት ያለው ባለይዞታ (Possessor) በመሬቱ ላይ ቤት ቢገነባ ወይም አትክልት ተክሎ መሬቱን ቢያለማው ይህ ባለይዞታ ለገነባው ቤት ወይም ለተከለው አትክልት ባለሃብት (owner) ይሆናል፡፡ ስለሆነም መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ የተገነባ ቤት እንዴት ዜጎችን የግል የንብረት መብት ሊያጎናጽፋቸው ይችላል የሚለው ጥያቄም ሊመለስ የሚገባው ከዚሁ አንጻር ሊሆን ይገባል፡፡ የቤት የግል ንብረት ባለቤትነት ባለቤቱ ቤቱን በሽያጭ ማስተላለፍን ጨምሮ ሌሎች የንብረት መብቶችን የሚሰጥ ሰፊ መብት ነው፡፡ እዚህ ላይ ልንመለከተው የሚገባው ጉዳይ አንድ የቤት ባለቤት የሆነ ሰው ሁለት መብቶችን አጣምሮ የያዘ ስለመሆኑ ነው፡፡ የመጀመርያው ቤቱን የገነባበት የመሬት ይዞታ መብቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በመሬቱ ላይ የተገነባው ቤት ባለቤትነት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህን ሁለት የንብረት መብቶች ለየብቻ ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉ ባይሆንም የመሬቱ ባለቤት መንግስት እና ህዝብ ሲሆን የቤቱ ባለቤት ደግሞ ቤቱን የገነባው የመሬት ባለይዞታ ግለሰብ ወይም ድርጅት ነው፡፡ ስለሆነም አንድ የቤት ባለቤት በይዞታ መሬቱ ላይ ቤት ሰርቶ ሲሸጥ ቤቱ እና ቤቱ የተሰራበት ይዞታ ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉ ባለመሆናቸው (intrinsic element) በመሆናቸው የይዞታ መብቱንም ጭምር በሽያጭ እንዳስተላለፈ ይቆጣራል፡፡
#የንብርት መብት
ማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ የግል ንብረት የማፍራት መብት እንዳለው፣ ይህ መብትም ንብረትን የመያዝ፣ በንብረቱ የመጠቀም፣ ንብረቱን በስጦታ፣ በውርስ ወይም በሽያጭ ወይም በሌላ ማኛውም መንገድ የማስተላለፍ መብቶችን የሚያጎናጽፍ ሰፊ መብት ሲሆን በህግም ጥበቃ የሚደረግለት መብት ነው፡፡
ይሁን እንጅ ይህ በህግ ጥበቃ የሚደረግለት ንብረት የማፍራት መብት የአብዛኛውን ህዝብ መብት ወይም ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል በህግ ሊገደብ አንደሚችል ከህገመንግስቱ አንቀጽ 40 በግልጽ መረዳት ይቻላል፡፡ የግል ንብረት ባለቤትነት መብት የሚመነጨው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ወይም ህጋው ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች በጉልበታቸው፣ በመፍጠር ችሎታቸው ወይም በካፒታላቸው ያፈሩት ሲሆን የንብረት መብት ይኖራቸዋል፡፡ ንበረት ግዙፍነት ያለው ሁኖ የሚንቀሳቀስና፣ የማይንቀሳቀስ ተብሎ ሊከፈል ይችላል(የፍ/ህ/ቁ 1127)፡፡
የመሬት ይዞታ መብት እና የቤት ባለቤትነት የንብረት መብቶች ግዙፍነት ያላቸው የንብረት መብቶች ሲሆኑ ከማይነቀሳቀሱ የንብረት መብቶች ውስጥ የሚመደቡ ናቸው (የፍ/ህ/ቁ 1030)፡፡ ይህም ሁለቱን መብቶች አንድ የሚያደርጋቸው የመጀመርያው ጉዳይ ነው፡፡
የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት ባለቤት መንግስት እና ህዘብ ብቻ እንደሆነ እና መሬትን መሸጥ በህግ የተከለከለ ስለመሆኑ በህገመንግስቱ ተደነግጓል፡፡ ዜጎች በመሬት ላይ ያላቸው መብት የመሬት ይዞታ መብት ሲሆን ከሽያጭ በስተቀር በመሬቱ ላይ የመጠቀም፣ የይዞታ መብታቸውን በስጦታ፣ በውርስና በኪራይ ለማስተላለፍ ይችላሉ፡፡ ይህ የመሬት ይዞታ መብትም እንደማንኛውም ግዙፍነት ያለው የንብረት መብት በህግ ጥበቃ የሚደረግለት ሰፊ መብት ነው፡፡
በሌላ በኩል የግል የቤት ባለቤትነት መብት ደግሞ ለሁሉም ዜጎች እና ህጋዊ ሰውነት ላላቸው ድርጅቶች በእኩልነት የተሰጠ መብት ሲሆን የቤት በለንብረት የሆነ ግለሰቦች ወይም ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች በቤቱ ላይ የመጠቀም፣ በስጦታ ወይም በውርስ የማስተላለፍ፣ የመሸጥ እና በሌላ ማንኛውም መንገድ ንብረቱን ለሌላ ወገን የማስተላለፍ መብት የሚሰጥ ነው፡፡
የመሬት ይዞታ መብት እና የቤት ባለቤትነት መብቶች መካከል ምን አይነት ግንኙነት ሊኖር ይችላል?
ቤት የሚገነባው በመሬት ላይ ነው፡፡ መሬት ደግሞ የመንግስት እና የህዝብ ነው፡፡ መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ የተገነባ ቤት እንዴት ዜጎችን የግል የንብረት መብት ሊያጎናጽፋቸው ይችላል የሚሉት ነጥቦች በዚህ ጽሁፍ ውስጥ የሚዳሰሱ ነጥቦች በመሆናቸው እንደሚከተለው ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡
#በመሬት ይዞታ መብት እና በቤት ባለቤትነት መብቶች መካከል ምን አይነት ግንኙነት ሊኖር ይችላል?
የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እና ዘላኖች መሬትን ለግጦሽም ሆነ ለእርሻ በነጻ የማግኘት እና ከርስታቸው ያለመነቀል ወይም ያለመፈናቀል መብት እናዳለቸው እንዲሁም የግል ባለሃብቶች በህግ በሚወሰን ክፍያ ከመንግስት መሬት ማግኘት እንደሚችሉ በህገመንግስቱ ተደንግጓል (አንቀጽ 40(4፣5፣6))፡፡ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እና ዘላኖች መሬትን በነጻ ከመንግስት የሚያገኙ ስሆን ሌላው ዘጋ ወይም ህዝብ ግን የመሬት ይዞታ መብቱን የሚያገኘው በክፍያ ነው፡፡ ይህ የህገመንግስቱ ክፍል ከአርሶአደሮች እና ዘላኖች በስተቀር ያሉትን ዜጎች በሃገሪቱ ማንኛውም የኢኮነሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የመሳተፍን እና በሃገሪቱ ሃብት እኩል የመጠቀም እና በእኩልነት የመልማት ህገመንግስታዊ መባታቸውን የሚገድብ መሆኑን ማስተዋል ይቻላል፡፡
ሆኖም ግን የመሬት ይዞታ መብት በነጻ ወይም በህግ በሚወሰን ክፍያ ከመንግስት የሚገኝ ሲሆን የቤት ባለቤትነት መብት ግን በግዥ፣ በስጦታ፣ በውርስ፣ ወይም በሌላ መንኛውም መንገድ የሚገኘ ሊሆን ይችላል፡፡ እዚህ ላይ ሊተኮርበት የሚገባው ጉዳይ ቤቱ የተገነባው መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ መሆኑ እና የተገነባውን ቤት ከመሬቱ ተነጥሎ ሊታይ የሚችል ንብረት አለመሆኑ ነው፡፡ ግንባታው ከመሬቱ ተነጥሎ ሊታይ የሚችል ካልሆነ ደግሞ የመሬት ይዞታ መብትን በህግ በተወሰነ ክፍያ ከመንግስት ተረክቦ ቤት የገነባ የቤት ባለቤት ባለቤት ያልሆነበትን መሬት ወይም በመሬቱ ጨምሮ በሽያጭ ማስተላለፍ እንደሚችል ለመገንዘብ የሚከብድ ጉዳይ አይደለም፡፡ ስለሆነም የመሬት ይዞታ መብትን እና የቤት ባለቤትነትን አንድ የሚያደርጋቸው ሁለተኛው ምክንያት የመሬት ይዞታ መብት ቤት ከተገነባበት በኋላ በሽያጭ ለሌላ ወገን ሊተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ እዚህ ላይ መሬትን በሽያጭ ማስተላለፍ እና የመሬት ይዞታ መብትን በሽያጭ ማስተላለፍ ግን ተመሳሳይ ትርጉም ሊሰጣቸው እንደማይችል ልብ ሊሉ ይገባል፡፡
መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ የተገነባ ቤት እንዴት ዜጎችን የግል የንብረት መብት ሊያጎናጽፋቸው ይችላል?
ከፍ ሲል እንደገለጽሁት መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ የመንግስት እና የኢትዮጵያ ህዝቦች ንብረት ነው፡፡ ይህም ማለት መንግስት ከሽያጭ በስተቀር መሬትን በሌላ ማንኛውም መንገድ ማስተላለፍ የሚችል ስለመሆኑ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ስለሆነም ዜጎች መሬትን ከመንግስት በነጻ ወይም በክፍያ የሚያገኙት ቢሆነም በዚሁ መሬት ላይ ያላቸው መብት ግን የመሬት ይዞታ መብት ብቻ ነው፡፡ ይህም ማለት ማንኛውም የመሬት ይዞታ መብት ያለው (Possessor) ሁሉ መሬቱን ከመሸጥ በስተቀር መሬቱን የመያዝ፣ በመሬቱ የመጠቀም፣ መሬቱን በስጦታ፣ በውርስ ወይም በኪራይ የማስተላለፍ መብቶች ሁሉ የሚያጠቃልል ነው፡፡
አንድ የመሬት ይዞታ መብት ያለው ባለይዞታ (Possessor) በመሬቱ ላይ ቤት ቢገነባ ወይም አትክልት ተክሎ መሬቱን ቢያለማው ይህ ባለይዞታ ለገነባው ቤት ወይም ለተከለው አትክልት ባለሃብት (owner) ይሆናል፡፡ ስለሆነም መንግስት እና ህዝብ ባለቤት በሆኑበት መሬት ላይ የተገነባ ቤት እንዴት ዜጎችን የግል የንብረት መብት ሊያጎናጽፋቸው ይችላል የሚለው ጥያቄም ሊመለስ የሚገባው ከዚሁ አንጻር ሊሆን ይገባል፡፡ የቤት የግል ንብረት ባለቤትነት ባለቤቱ ቤቱን በሽያጭ ማስተላለፍን ጨምሮ ሌሎች የንብረት መብቶችን የሚሰጥ ሰፊ መብት ነው፡፡ እዚህ ላይ ልንመለከተው የሚገባው ጉዳይ አንድ የቤት ባለቤት የሆነ ሰው ሁለት መብቶችን አጣምሮ የያዘ ስለመሆኑ ነው፡፡ የመጀመርያው ቤቱን የገነባበት የመሬት ይዞታ መብቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በመሬቱ ላይ የተገነባው ቤት ባለቤትነት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህን ሁለት የንብረት መብቶች ለየብቻ ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉ ባይሆንም የመሬቱ ባለቤት መንግስት እና ህዝብ ሲሆን የቤቱ ባለቤት ደግሞ ቤቱን የገነባው የመሬት ባለይዞታ ግለሰብ ወይም ድርጅት ነው፡፡ ስለሆነም አንድ የቤት ባለቤት በይዞታ መሬቱ ላይ ቤት ሰርቶ ሲሸጥ ቤቱ እና ቤቱ የተሰራበት ይዞታ ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉ ባለመሆናቸው (intrinsic element) በመሆናቸው የይዞታ መብቱንም ጭምር በሽያጭ እንዳስተላለፈ ይቆጣራል፡፡