የኛ ግጥም
44 subscribers
2 photos
2 links
#Kehas

#For business

#gitm

#Tarik

#Feta 😁

#Zena😍

#Sak😀

#desta😇
Download Telegram
😘የከንቲባው ልጅ😘

🔥ክፍል 18


.
.
.
በሩን አልፌ የመሄድ አቅም አልነበረኝም ። ዘጋሁትና ወደሷ ተመልሼ እቅፌ ውስጥ አስገባዋት ። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች ፤ ሁለመናዋም ይንቀጠቀጣል ። 'እሽሽሽ ፡ በቃ አታልቅሺ ፣ በየትኛውም ጊዜና ቦታ ካንቺ ጋር ነኝ ። ትቼሽ የትም አልሄድም ። ሁሉንም ችግሮችሽን ላላስወግድልሽ እችላለሁ ፤ ነገር ግን ብቻሽን እንድትጋፈጪው በፍፁም አላደርግም' አልኳትና ዕምባዋን ጠራርጌ ፡ ግንባሯን ፣ አይኗን ፣ ጉንጯንና አንገቷ ስር ስሜያት ተያይዘን ወደ ቤት ተመለስን ። ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ዘንድሮ ባወጣው ህግ መሠረት የ #3 ቀን ቀሪ ከጊቢው ያሰናብታል ። የኔ ቀሪ ደግሞ ከዚያ እያለፈ ስለሆነ ትንሽ አሳስቦኝ እንጂ መጀመሪያውኑ የትምህርት ፍቅር ኖሮኝ አይደለም ወደ ጊቢ ለመመለስ የተነሳሁት ። ይሄው አሁን ትምህርቱ ላይ ፈርጄ የከንቲባው ልጅ ቤት ቀርቻለሁ ። ትውልድ ይዳን ፤ ትምህርት በኔ ይብቃ ። ሳስበው ግን ህይወት በዚሁ ሁኔታ ከቀጠለች ወደፊት ልጄን ትምህርት ቤት ወስጄ የማስተምረው አይመስለኝም ። ለነገሩ ልጄ እንደኔ ደደብ ፣ ደነዝ እና ሰነፍ የሚሆን አይመስለኝም ። በኔ ከወጣ ግን ውሃ በላው ። Campus ባይገባ ነው የሚሻለው ። ልግባ ቢል እራሱ ማን ሲያስገባው ...? ከኔጋር እየኖረ ትምህርቴን ማቄን ምናምን የሚል ከሆነ #18 ዓመት እስኪሞላው ደረስ አልጠብቅም ። ልክ ይቺን ጥያቄ ስያነሳ በሬን ከፍቼ ካለኝ ንብረት ላይ የድርሻውን ሰጥቼው አሰናብተዋለው ። (ንብረት ግን የሚኖረኝ አይመስለኝም ... ። የኔ ነገር ፡ ለራሴም ሳልሆን የልጄን ፈተፈትኩ አይደል ። (አንተ ልጅ ግን ልጅ አለህ እንዴ ...?። ምን ላርግ ፡ ከ #3 ወር በፊት የተፈተነው Applied Maths final ፈተና ትዝ ብሎኝ እኮ ነው ። On time #02:00 ሰዓት ሻርፕ (flat ...) ላይ class ተገኘሁና አሰላለፍ አሳምሬ አስተማሪውን ጠበቅነው ። ዛሬማ ካልደፈንኩት ከዚህ ክፍል ውስጥ ንቅንቅ አልልም ብዬ ቆረጥኩ ። በስተ ሰሜን ጎበዙ የዶርሜ ልጅ ፣ በስተ ደቡብ ከዋላዬ ስለሆነ አይመቸኝም ፣ በስተ ምስራቅ ከክፍል #1ኛ ውጤት ያለው ልጅ ፣ በስተ ምዕራብ ደግሞ ከዲፓርትመንታችን ከፍተኛ ውጤት ያመጣው ልጅ ተቀምጠዋል ። Morino እራሱ አሰላለፍ እንዲህ አይችልበትም ። የተከተልኩት የጨዋታ ስልትም ፡ ትንሽ ማንበብ + ብዙ መኮረጅ = #50/50 የሚለው ነው ። ኩረጃ ላይ ብዙም ልምድ የለኝም ። እንግዲህ የኔ ጉድ ዛሬ ይታያል ። (ጉድ = Good ...) ፈታኙም ፈተናውን ይዞ ከተፍ አለ ። (ምናለበት አሁን ቢቀር ይሞታል ...?) ። ፈተናውን ጠረጼዛ ላይ አስቀመጠና እንዲህ አለን "Continous ከ #50 ሁላችሁም ከ #40 በላይ ስላመጣችሁ አይያዝም ። ስለዚህ የዛሬው ፈተና የሚያዘው ከ #100% ነው ። #90 ጥያቄ ተዘጋጅቷል ፣ ለእያንዳንዱ ጥያቄ #3 pharagraph ትፅፋላችሁ ። ሁሉም ጥያቄ የወጣው ከተማራችሁት ውጪ ሲሆን ፤ ጥያቄዎቹ እንኳን ለእናንተ ለኛም አዲስ ናቸው ። የቀረው #10% ነጥብ ደግሞ ስማችሁን በቻይንኛ መፃፍ ይሆናል ። አሁን ፈተናውን እንጀምራለን ልክ ጀምሩ እንዳልኳችሁ pencil down እላቹዋለው ታቆማላችሁ ። ፈተናው ላይ #1 ኤክስ የገባበት ተማሪ ከጊቢው ይሰናበታል ። መልካም ፈተና ። ነጮች "ስለ ሰው ይበልጥ ባወክ ቁጥር ውሻህን ትወደዋለህ" ይላሉ ። እኔ ግን እላቹዋለው 'ስለ Maths ይበልጥ ባወክ ቁጥር አለመማርን ትወዳለህ' ።...

ከከንቲባው ልጅ ጋር ቲቪ ከፍተን እያየን እያለ ስልኬ ላይ Msg ገባና አውጥቼ ሳየው Cost ገብቶልኝ ነው ። Non cafe ስለሆንኩኝ እንደ ተለመደው መንግስት #450 የኢትዮጵያ Dollar ባንክ account ላይ አስገብቶልኛል ። እኔ የምለው ግን ፡ መንግስት ለካ እንዲህ ቋጣሪ ነው ። cost መግባት የነበረበት በየወሩ በ #28 ነበር ። የዚህኛው ወር ግን በ #36ኛው ቀን ነው የገባው ። ቆይ ግን #450 ብር ለ #1 ወር በዚህ ኑሮ ፡ ብር ሆና ነው የምትበላው ...? ያውም ከተማሪ ። እኛኮ ለምሳ እና እራት ብቻ #1200 ብር ነው የምንከፍለው ። እነሱ ግን የ #5 ሚሊዮን ብር እራት በልተው ፤ በ #450 ብር መፋቅያ ጥርሳቸውን ይፍቃሉ ። Bisrat tv እያየን ነው ። ፕሮግራሙም ስለ ሶሪያ ህፃናት ነው ። አንድ የ #7 ዓመት ህፃን እንዲህ እያለ ነው "በሽር አል አሳድ'ን (የሶርያ president) ምን አደረግነው ...? ዝምብለን እየኖርን ነበር ። ምንም ሳናደርገው ቤታችንን አፈራረሰብን ፣ ቤተሰቦቻችንን እንዳለ ገደላቸው ። ቆይ ግን ምን አድርገነው ነው ...?" ። ይሄንን ሲናገር ፊቱ እንደ ጎርፍ ዝናብ በዕምባ ተሞልቶ ነበር ። ሶሪያ ውስጥ የሞቱት ህፃናት ብቻ ከ #50,000 በላይ ናቸው ። አብዛኛዎቹ ሀገር ሰላም ብለው የትምህርት ገበታ ላይ የነበሩ ታዳጊዎች ናቸው ። በራሳቸው ጥፋት ሳይሆን በአባቶቻቸው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት ነገን ሳያዩ ዛሬን ሳይኖሩ በአጭር የተቀጩ ህፃናት ። ዛሬም ድረስ ጦርነቱ ቀጥሏል ፣ ሀገሪቷ ምድረ በዳ ሆናለች ፣ የሶሪያ ህፃናትና ህዝቦችም ስደት ላይ ናቸው ። አሸናፊ የሌለው የእርስ በእርስ ጦርነት መጨረሻው እንግዲህ ይህ ነው ። ከወር በፊት ሳቢያን ፡ ድሬዳዋ ብር ለማውጣት ባንክ ቤት ስሄድ መንገድ ላይ የሶሪያ ስደተኞች ተቀምጠው ሲለምኑ አይቼ ነበር ። ባልና ሚስት መሀላቸውን ልጃቸውን አስቀምጠው ፊትለፊት ደግሞ በአማርኛ ፊደል የተፃፈ "የሶሪያ ስደተኞች ነን ፡ እባካችሁን እርዱን" የሚል Copy ወረቀት ተቀምጦ ፣ በዚያ በኩል የሚያልፍ ሰው ደግሞ ከንፈሩን እየመጠጠላቸው ያለውን #1 ፣ #5 ፣ #10 ብር እየሰጣቸው ያልፍ ነበር ። እኔም ሳያቸው አንጀቴን ነበር የበሉኝ ። በተለይ ደግሞ መሀላቸው የተቀመጠው ፣ ምንም የማያውቀው ፣ #4 ዓመት እንኳን ያልሞላው ህፃን ልጅ እንዴት እንደ ሚያሳዝን ። anyways አያድርገውና ኢትዮጵያን ሳስባት እንደ ሶሪያ ካልሆንኩኝ ሞቼ እገኛለሁ ያለች ትመስላለች ። ሰላም ስልችት ብሏት ደም ደም ከሸተታች ሰነባብታለች ። ሰላም ሲሆን ጀርባዋን ይበላታል መሰለኝ ግደል ግደል ፣ ሰልፍ ውጣ ሰልፍ ውጣ ፣ ኮብል ኮብል ፣ አፍርስ አፍርስ ፣ ረብሽ ረብሽ ፣ ወዘተ ወዘተ ይላታል ። (ወዘተ ወዘተ እንኳን አይላትም ...) ። ከሶሪያ እንኳን መማር አልቻለችም ፤ የሰላም ዋጋ ምኑም አልገባትም ። ዛሬ ሁላችንም በየቤታችን ሆነን የምናየው የሶሪያ መጨረሻ የሌለው ዕልቂት ፣ መድረሻው የማይታወቅ ስደት ፣ መልስ የማያገኝ ጥያቄ ፣ ቀስ በቀስ የኛው ታሪክ ሆኖ ዓለም በየቤቱ ቁጭ ብሎ ይታዘበናል ። ልክ ዛሬ ለነዚህ ስደተኞች ከንፈር እየመጠጥን ሳንቲም እንደ ወረወርን ፤ አንድ ቀን ደግሞ ለኛም በባዕድ ሀገር ይወረወርልን ይሆናል ። ይሄ እንዳይሆን ከፈለግን ሁሉን ነገር የመንግስት ስራ ነው ማለቱን ትተን ለሰላማችን ስንል እራሳችን ፣ ቤተሰባችን ፣ ጓደኛችን ፣ ጎረቤታችን ፣ ሰፈራችን ፣ ቀበሌያችን ፣ ወረዳችን ፣ ዞናችን ፣ ክልላችን ፣ ምናምን ሳንል ለአንዲት ሀገራችን በጋራ ብንሰራ የተሻለ ብቻ ሳይሆን ተመራጭም ይሆናል ።....
​​🌺የከንቲባው ልጅ🌺

🔥ክፍል 30


.
.
.
ድሬዳዋ በሰላም ገብተ

​​ናል ። ህይወት "ከልደትህ ቀን ላይ አንድ ሰዓት ሰጥተኸኝ ለትንሽ ጊዜ እንኳን አብረኸኝ አትሆንም ...?" አለችኝ ወደ ጊቢ እንደምሄድ ስነግራት ። ያንን አሳዛኝ ፊቷን እያሳየችኝ ስትለምነኝ ጥያት የመሄድ ምንም አቅሙም አይኖረኝም ። የድሬ ከተማ መግቢያ ላይ ወደ ሚገኘው #CCECC ሆቴል አመራን ። የቻይናዊ ሰው ሆቴል ነው ። "ከዚህ በፊት እዚህ መጥተህ ታውቃለህ እንዴ ...?" አለችኝ አየመራዃት ወደ ውስጥ ስንገባ ። 'አዎ' ስላት "መቼም የቻይና ምግብ አምሮህ እንዳልመጣህ ተስፋ አለኝ" አለችኝ እያሾፈችብኝ ። 'አይደለም ፤ ፊልም ለመስራት ነው የመጣሁት' አልኳት ። "የድሬ ልጅ ነች የከዚራ ፤ ስለ ውበቷ ስንቱን ላውራ የሚል ፊልም መሆን አለበት" አለችኝ በድጋሜ እየቀለደችብኝ ። 'ርዕሱን ለጊዜው አላውቅም' ስላት "እንዴዬ ፡ አንተ የምርህን ነው እንዴ አለችኝ" ኮስተር ስላልኩባት ። 'አዎ የምሬን ነው ። እንደውም አምስት ወር ሊሆነው #4 ቀን ይቀረዋል ። ታህሳስ #22 ነበር ። እዚሁ ሆቴል ውስጥ በአክተሮች ፣ ካሜራ ማኖች እና ሜክ አፕ አርቲስት ተከብቤ ነበር ። ቃልኪዳን ጥበቡ (የባባ ሚስት) ፣ ከዘመን ድራማ ተዋናዮቹ እነ አዩ ግርማ ፣ ሄኖክ ድንቁ ፣ እና የመሳሰሉት ነበሩ የፊልሙ ተዋናዮች ። ለካ ፊልም እንደዚህ ተቀርፆ ነው እኛ ጋር የሚደርሰው ። ብታይ የአምስት ደቂቃ ትዕይንት ለመቅረጽ ከሃያ ጊዜ በላይ ነው Cut ፣ action የተባለው ። ከስምንት ሰዓት እስከ #11 ሰዓት ቁጭ ብዬ ሲቀረፅ ያየሁት የ #10 ደቂቃ ትዕይንት አትሆንም ። ፊልሙ ድሬ ብቻ ሳይሆን ሀረርም እንደሚቀረፅ ነግረውኛል' አልኳት ። "መቼም የፊልሙ አክተር አንተ መሆን አለብህ" እያለች ትስቃለች ። 'በመጀመሪያ ደረጃ በዘመድ ነው famous የሆንከው እንዳትይኝ እንጂ ፤ የፊልሙ producer የዶርሜ ልጅ ጓደኛ በመሆኑ ነው እዛ የመሄድ እድል ያገኘሁት ። በመቀጠል ደግሞ እኔን የፈለጉኝ ፊልሙ እዚህ ሆቴል ውስጥ ሲቀረፅ በአክተሮቹ ጀርባ ከሆነች ልጅ ጋር ቁጭ ብዬ ሻይ እንድጠጣ ነው' ስላት ሳቋን በሀይል ለቀቀችውና አስተናጋጁ ሳንጠራው ደንግጦ መጣ ። ምሳ ሰዓት እስኪደርስ እስከዚያው ለስላሳ አምጣልን አልኩትና ተመልሶ ሄደ ። ማፌዟን አላቆመችም ። "እና ይሄን ሁሉ part ሸፍነህላቸው ስንት ብር ከፈሉክ ...?" አለችኝ ። 'እኔ ከጥበብ ገንዘብ አልቀበልም' ስላት "owk የፊልሙ ፕሮዲዩሰር ስም መሆኑ ነው ጥበብ" አለችኝ ። ህይወት በመሆኗ ነው ዕድለኛ የሆነችው እንጂ ሌላ ሰው ፤ በተለይ ደግሞ ወንድ ቢሆን እንደዚህ የሚመልስልኝ እዚሁ ነበር ሰይፌው የምሄደው ። (ወንድ ልጅ አይኑር ያለው ማነው ...?😳) ። በኔ ላይ የመቀለድ ፣ የማሾፍና የማፌዝ መብት ያላት ብቸኛዋ ሴት እሷ ሆናለች ። እሷን የመቀየም ፣ የማኩረፍና በሷ ላይ የመናደድ አቅም የለኝም ። እራሷ ናት ያሳጣችኝ ። ስትስቅ ፣ ስትደሰት ፣ ሁሉን ነገር ረስታ ቀልቧን ሁሉ ስትጥልብኝ በህይወት በመኖሬ እደሰታለሁ ። ፈገግ ባለች ቁጥር የሷን ብቻ ሳይሆን የኔንም ዕድሜ በዕጥፍ ትጨምራለች ። በተለይ ደግሞ "የኔ ጌታ" እያለች ስታቆለጳጵሰኝ ሰማይና ምድሩን እኔው እራሴ በእጄ ጠፍጥፌ የሰራሁላት ነው የሚመስለኝ ። ስታዝን ፣ ስትጨነቅ ፣ ስታለቅስ ፣ ስታኮርፍ ፣ ህይወት ግልብጥብጥ ስትልባት ፣ በቃ ያኔ ነው በህይወት መኖሬን የምጠላው ። ከእሷ አይን የምትፈስ እያንዳንዷ የዕምባ ዘለላ ከእሳተ ገሞራ በላይ ውስጤን የማቃጠል ሀይል አላቸው ።

'ፊልም መስራት የልጅነት ህልሜ ነው ። ትዝ ይለኛል የ #1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ እያለሁ ነበር የወሰወሰኝ ። ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ተማሪ እያለሁና በትምህርት ቤትም ብዙ የመድረክ ድራማዎችን ሰርቼ ነበር ። አሁንም ድረስ የኔ የወደፊቱ ህልሜ በመካኒካል ኢንጅነሪንግ ተመርቄ ስራ መስራት ይቅርታ ስራ ማፈላለግ አይደለም ። የፊልም አክተር መሆንና መሆን ብቻ ነው እቅዴ ። ከፊልም ውጪ plan B እራሱ የለኝም ። ፍላጎቴ ብሩና ዝናው አይደለም ። ፊልም መስራቱን ብቻ ነው የምፈልገው ። መንገድ ላይ የፊልም director ባገኝ እግሩ ላይ ወድቄ ከፈለክ በነፃ #10 ፊልም እሰራልሀለው ማለቴ አይቀርም' ስላት "እሺ የኛ shah rhuk Khan" አለችኝ ህይወት ትኩር ብላ ካዳመጠችኝ በዋላ ። በነገራችን ላይ የፊልም አፍቃሪ እንድሆን ያደረገኝ የህንዱ አክተር ሻህሩካን ነው ። የሱን ታሪክ በጣም ስለምወደው አጠር አርጌ ልንገርሽ አልኳትና ለትረካው ተሰናዳሁ ። "በልጅነቱ ጎበዝ ተማሪ ነበር ። ስፖርት በተለይ ደግሞ ኳስ መጫወት በጣም ይወዳል ። በልጅነቱ ትምህርት ቤት እያለ አንድ ቀን አስተማሪያቸው ወደ ፊት አወጣውና ስታድግ ምን መሆን ትፈልጋለህ ብሎ ጠየቀው ። እሱም አፉን ሞልቶ በኩራት የቦሊውድ ምርጥ አክተር እሆናለሁ አለው ። ክፍል ውስጥ የነበሩ ሁሉም ተማሪዎች ሳቁበት ። አስተማሪውም የማይሆን ህልም እንደሆነና ሀሳቡን ቀይሮ ትምህርቱ ላይ ብቻ እንዲያተኩር ነገረው ። ለሻህሩክ ግን ይህ አልተዋጠለትም ። ህልሙን እውን ለማድረግ የ #2ኛ ዲግሪ ትምህርቱን አቋረጠና ወደ ፊልም ጉዞ ጀመረ ። ነገር ግን በዛ ሰዓት ሁለት ነገሮች ፈተና ሆኑበት ። የመጀመሪያው ወላጆቹን በሞት ማጣቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ታላቅ እህቱ የአይምሮ ህመምተኛ መሆኗ ነበር ። በዛ ምክንያት ቤተሰቦቹን የማስተዳደር ሀላፊነት እሱ ላይ ወደቀ ። ከድህነት ጋር ትግል ገጠመ ። ስራ ለመፈለግ ወደ ሙምባይ ከተማ ሄደ ። የቤት ኪራይ የሚከፍለውን አጥቶ ከቤት ተባሮ ሁለት ቀን ጎዳና ያደረበት ቀን ነበር ። የሰዎች ሱቅ ስር ያደረበት ቀን ደግሞ ስፍር ቁጥር የላቸውም ። ሆኖም ግን በዚሁ ችግር ውስጥ ሆኖ ተዋናዮች የማይደፍሩትን ትወናዎች ይሞክር ነበር ። የሆነ ቀን ለመወዳደር ሄዶ የፊልሙ director "አንተ አርቲስት የምትሆን ሰው አይደለህም" አለው ። እሱ ግን ምንም ሳይመስለው ትቶት ሄደ ። ግን ተስፋ አልቆረጠም ፤ ወደዋላም አልተመለሰም ። ሁልጊዜ ወደ ህልሙ በሚወስደው መንገድ ላይ ይረማመድ ነበር ። ያለምንም ክፍያ ሲኒማ በር ላይ ቆሞ የመግቢያ ticket ይሸጥ ነበር ። በወረደ ሂሳብ እንደ ካሜራና መብራት ያሉ የፊልም መሳሪያዎችን ተሸክሞ ከአርቲስቶች ዋላ ይሄድ ነበር ። ነገር ግን አንድ ቀን መጣ ። የሱ ቀን ። የለውጥ ቀን ። ትንሽ ብር ተከፍሎት አንድ ፊልም (#Deewana) እንዲሰራ ተነገረው ። ከዛው ላይ ተነሳ ፣ ቀጠለበት ፣ ድህነትን ማሸነፍ ጀመረ ፣ እውቅና ትከተለው ጀመር ፣ ህልሙም እውን ይሆን ጀመር ። ለአርት አትሆንም የተባለው ሰው ምርጥ አክተር መሆን ጀመረ ። ዛሬ እንደ ህንድ ብቻ ሳይሆን እንደ አለም በጣም ታዋቂና ዝነኛ አክተር ነው ። በድህነት የሰዎች ቤት ስር ያድር የነበረው ዛሬ ላይ ከአለማችን ሀብታም አክተሮች መሀል አንዱ ነው ። ከብዙ ተቋማት ብዙ ሽልማት ያገኘ ፣ ከራሱም ተርፎ ለህዝቡ የደረሰ ጀግና ነው" ። እናም የኔ ህይወት ሰው ትሆኛለሽ ፣ አትሆኝም ስላለሽ አይደለም ። እሆናለሁ ካልሽ የማትሆኝው የለም ። ዋናው ለምንፈልገው ነገር እስከመጨረሻው ድረስ መስዋዕትነት መክፈል ነው ። ትግልሽን አሪፍ ካደረግሽ ብትወድቂ እራሱ አንድ ቀን ከላይ መሆንሽ አይቀርም ።

ይቀጥላል...