የኛ ግጥም
45 subscribers
2 photos
2 links
#Kehas

#For business

#gitm

#Tarik

#Feta 😁

#Zena😍

#Sak😀

#desta😇
Download Telegram
🌺የከንቲባው ልጅ🌺

🔥ክፍል 14


.
.
.
ብዙም አልተኛሁም ነበር ። በትካዜና በሀዘን እንደ ዳግም ምፅአት የራቀኝ ለሊት ነጋ ። የኔስ ይሁን የራሴ ችግር ነው ። የከንቲባውን ልጅ ግን ለማዝናናት ይዤ መጥቼ ቀኗን አበላሸሁ ። ጠዋት ከእንቅልፍ ሳይሆን ከአልጋው ላይ ስነሳ "ደና አደርክ የኔ ጌታ ፡ ቁርስ ቀርቧል እሺ ቶሎ ፊትህን ታጥበህ ና" አለችኝ ። ቁርሱን ከበላን በዋላ 'ትናንት እንደዛ ስለ ሆንኩብሽ በጣም ይቅርታ' ስላት "ኧረ አያሳስብም ፡ እኔ ከዛ በላይ ሆኜብህ አልነበር እንዴ ፡ ባይሆን ካሁን በዋላ እንደዛ አትሁን እሺ ፡ የሰውን እምባ ጠርገው እያሳሳቁ የምን ለራስ ማልቀስ ነው ...?" አለችኝ በአሽሙር መልክ ። ቀጥላም "ካሁን በዋላ እንደውም ከቴዲ አፍሮ ሙዚቃ #ማራኪዬ የሚለውን ሳይሆን #መማፀኔ የሚለውን መውደድ ያለብክ ይመስለኛል" አለችኝና ድምጿን ከፍ አድርጋ ዘፈኑን ታዜምልኝ ጀመር ።

"በደለኛ ሰው ይቅርታ ብሎ አንሶ ሰው ከካሰ ፡
ይኖር ወይ ልቡን ያልመለሰ ፣
ሳይገባኝ ለኔ ፡ የቱጋ እንደሆን እንኳን ማስቀየሜ
ተይ ብያት ነበር ባለኝ አቅሜ ።
መማፀኔ ፡ ማሪኝ ማለቴ ፡
ለኔስ ሳይገባኝ ነው ጥፋቴ ፣
ታድያ እንዴት ይሆን ፡ ወዳጅን ነግሮ ፡
ልብን መመለስ ወደ ድሮ" ።

ቆሜ ነበር ያጨበጨብኩላት ። ስትዘፍን ድምጿ ስያምር ። በቃ ሴቷ ቴዲ አፍሮ ብያታለሁ ። "ከቤት ስለማልወጣ ስዕልና ሙዚቃ እቤት ውስጥ እሞክራለሁ ። እስካሁን አባቴ ከሰጠኝ ስጦታዎች መካከል በጣም የምወደው ጊታር'ን ነው ። ሲከፋኝና ብቸኝነት ሲሰማኝ በጊታሬ እዘፍናለሁ ። አንተ ከመጣህ ወዲህ ብቸኝነት ስላልተሰማኝ ነው እሺ ጊታሩን አውጥቼ ያልተጫወትኩት" አለችኝ እያሾፈችብኝ ። ከዛን "ስማኝማ ፡ ዛሬ ማክሰኞም አይደል ፡ ደብረ ዘይት ላይ የመጨረሻ ቀናችን እኮ ነው ። ታውቃለህ አባዬ ባለፈው ሀሙስ ነበር ሳምንት እመለሳለሁ ብሎ የሄደው ። እና ሳምንቱ ደግሞ ከነገ ወዲያ ስለሆነ ነገ ወደ ድሬዳዋ መመለስ ይኖርብናል" አለችኝ ። በግልጽ ባትነግረኝም ለማለት የፈለገችው ነገር ገብቶኛል ። የዙሪያ ጥምጥሙ ፍቺ ፈታ እንበል የሚል መሆኑ ነው ። ከዛ በፊት ግን ልጠይቃት ብዬ የረሳሁትን ነገር የአባትዋን ስም ስታነሳ ትዝ አለኝ ። 'ስሚማ ፡ አባትሽ ግን ለምን ይሄን ሁሉ ዓመት ለብቻሽ በአንድ ቤት ውስጥ እንዳስቀመጠሽ እኮ በግልጽ አልነገርሽኝም...? ፡ ማለቴ አባትሽ በስልጣኑ ምክንያት ከሰዎች ጋር ችግር ውስጥ ገብቶ አንቺላይ ጥቃት እንዳይደርስ ከፈራኮ አንቺን በአንድ ቤት ውስጥ ከማስቀመጥ ይልቅ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ይችል ነበር ' አልኳትና ጠየኳት ። እሷም "የመጀመርያው ፡ አባቴ ብቻውን ስላሳደገኝ ፣ ከኔ ውጪ ማንም ስለሌለውና ከኔ ተለይቶ መኖር ስለማይችል ነው ። ሁለተኛው ፡ ውጪ ቢልከኝም እዛ ማንም ስለሌለን ከፈረንጅ ነፃነት የሀገር ውስጥ እስረኛ መሆን ይሻላል ብሎ ነው ። ያው 'ከማያውቁት መላክ ፡ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል' ይባልም የለ ። ሲጀምር እሱ ሂጂም ቢለኝ ከሱ ተለይቼ ውጪ ሀገር መኖር አልፈልግም" አለችኝና ሶስተኛው ብላ ልትቀጥል ስትል 'ኧረ ይበቃል ፡ ሶስተኛ ፣ አራተኛ እያልሽ ከቀጠልሽማ ሳንዝናና መሽቶ መንጋቱ ነው' አልኳትና ይዣት ተነሳን እና ከአንዱ ምግብ ቤት ገብተን ምሳ ከበላን በዋላ "ፍቅር ግን ለአንተ ምንድነው...?" አለችኝ የከንቲባው ልጅ በልጅቷ የቅድሙ መልስ እንደኔው ተገርማ ። 'እርግጠኛ ነኝ ሁላችንም ብያንስ አንድ ጊዜ አፍቅረናል ። እንደውም አብዛኞቻችን የፍቅርን ትርጉም ሳናውቅ ነው ያፈቀርነው ። anyways ፍቅር ግን ለኔ ...! አንድ ወንድና ሴት ተፈላልገው የሚመሰርቱት ግኑኝነት ...? ፡ እሱ ነው ፍቅር ...? ፡ አይመስለኝም ። እስቲ ወይ የራስሽን ወይንም ደግሞ የጓደኛሽን የፍቅር ታሪክ ለትንሽ ደቂቃ አስቢው ። እያሰብሽው እንደሆነ ተስፋ አለኝ ። እርግጠኛ ሆኜ የምነግርሽ እራሳችንን ወደን እንጂ ሰውን አፍቅረን አናውቅም ። እንዴት...? ለምትዪኝ :- በመጀመሪያ ወንድ ከሆነ አንዲት ሴትን ፡ ሴት ከሆነች ደግሞ የሆነ ወንድ ፡ በሆነ አጋጣሚ ያገኛሉ ። የሆነ ነገሯ ይማርከዋል ፡ #90% መልኳ ፣ አካሄድ ፣ አለባበስ ፣ አነጋገር ፣ ወዘተ ። ይተዋወቃሉ ፡ ሊግባቡም ላይግባቡም ይችላሉ ። ጉዳዩ እሱ አይደለም ። ከጥቂት ቀናት በዋላ ፡ ካላገኘዋት ፣ እጄ ካላስገባዋት ፣ የኔ ካልሆነች ፣ ህይወቴ ካለሷ ባዶ ነው ፣ ወዘተ ማለት ይጀምራል ። እዚህ ጋር ልብ በይ እንግዲህ ። አነዚህን ነገሮች እያለ ያለው ለልጅቷ አስቦና ተጨንቆ አይደለም ፡ ለራሱ ፍላጎት እንጂ ። ስለናፈቀችው ፣ ደስ ስላለችው ፣ ስለምታምር ፣ ከሷ ጋር ከሆነ ደስተኛ እሆናለሁ ብሎ ስለሚያስብ ፣ ባጠቃላይ ልጅቷ ትሆነኛለች ብሎ እንጂ ፡ ለልጅቷ እሆናታለው ፣ ብሎ አይደለም ። አስተውይ ፡ መጀመሪያ ላይ አፈቀርኳት ብሎ ሲያወራ የሱ ህይወት ካለሷ ባዶ ሆኖ ስለተሰማው እንጂ የሷ ህይወት አሳስቦት አይደለም ። የሱ ጭንቀት እንጂ የሷ ፍላጎት አልታየውም ፤ አያውቅምም ። በቃ በዛ ሰዓት እሱ የሚፈልገው ነገር ቢኖር ልጅቷ የሱ እንድትሆን ነው ። የሱ ብቻ ። እሷ እንኳን የሌላ ሰው ሆና ማየቱ ይቅርና ሰላም እንኳን ቢሏት ካልገደልኳቸው ሊልም ይችላል ። እሷን ከራሱ ውጪ ከሌላ ሰው ጋር ለሴኮንድ እንኳን ማሰብ አይፈልግም ። እሷ አልፈልግህም ብትለው እንኳን በግድ ካልሆንሽ የሚል ጉድ ውስጥም ሊገባ ይችላል ። አስቢ ይሄን ሁሉ እያደረገ ያለው ለራሱ ሲል ነው ። ይሄንን ነው እንግዲህ ፍቅር ብለን የጠራነው ። እመኚኝ ግን ከዚህ ሰው በላይ እራስ ወዳድ ሰው በምድር ላይ የለም ። የፍቅር ትርጉም ግን ይህ አልነበረም ። ፍቅር ከራስ አልፎ ለሰዎች ሁሉ መኖርና መሞት ነው ። ቢተያዩም ባይተያዩም ፣ ብታምርም ባታምርም ፣ ለሱ ህይወት አስፈላጊ ሆነች አልሆነች ፣ እውነተኛ ልብ ካለው ያኔ የእውነት ፍቅር ከልቡ ይገባል ። በአይኑ ሳይሆን በልቡ ማየት ሲጀምር እሱ ሳይፈልገው ቤቱ ድረስ መጥቶለት ደጁን ያንኳኳል ። አፍቃሪ መሆን ከፈለገ ከልቧ ውጪ ምኗንም ሳያይ ፣ ምንም ሳታደርግለት ፣ ብትበድለው ብትክሰው ፣ ለሱ ሆነች አልሆነች ፣ ባጠቃላይ የሷ ነገር አሳስቦት እንጂ የሱ ጎዶሎነት ተሰምቶት አይውደድ ። ለጎዶሎው ብሎ ካፈቀረ አንድ ቀን እንዳልተሟላለት አስቦ ሊተዋት ይችላል ። የሷን ጎዶሎ ሊሞላ ቢሯሯጥ ግን አትራፊ ይሆናል ። ቅዱሱ መፅሐፍም "ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" አይደል የሚለው ። ክርስቶስስ ከሰማይ ላይ ወርዶ የሰውን ስጋ የለበሰው ለራሱ ጥቅም ይመስልሻል ...? ፍቅር መጠቀም ሳይሆን መጥቀም ነው ። እውነተኛ አፍቃሪ በነገሮች ሁሉ ቅድምያ ለራሱ ሳይሆን ለሌላ ሰው ሰጥቶ የሚጠቅም እንጂ የራሱን ችግር ለማሸነፍ ብሎ በሌሎች የሚጠቀም አይደለም...
"አንተ ልጅ ግን ሰባኪ ነገር ነህ እንዴ ...?" አለችኝ ሳወራላት የነበረውን ሁሉ በተመስጦ አይን አይኔን ትኩር ብላ እያየችኝ ከሰማችኝ በዋላ ። ቀጥላም "ቆይ ግን አንተ ሴት ልጅን መተህ አታውቅም ...?" አለችኝና ብዙ ዓመት ወደዋላ እንድመለስ አረገችኝ ። 'ትዝ ይለኛል እንደ ትናንት ፡ ከ #10 ዓመት በፊት በ #2001 ዓ.ም #4ኛ ክፍል እያለሁ ነበር ። #6ኛውን period ተምረን ተደወለ ። ምሳ ሰዓት በመሆኑ ፣ እቤታችንም ለት/ቤቱ ቅርብ ስለነበረ ወደ ቤት ለመግባት ቦርሳዬን ይዤ ከ desk ላይ ተነሳሁ ። ነገር ግን አጠገቤ ትቀመጥ የነበረችው አቢጊያ የምት