የኛ ግጥም
45 subscribers
2 photos
2 links
#Kehas

#For business

#gitm

#Tarik

#Feta 😁

#Zena😍

#Sak😀

#desta😇
Download Telegram
🌺የከንቲባው ልጅ🌺

🔥ክፍል 12
.
.
.
.
'በኛ ካምፕ ውስጥ ደግሞ አንድ ታሪኩ ብቻ ነበር ያለው ፤ እሱም ምርጥ ጓደኛዬ ነበር ። ከዛን ልጆች እሱን ጠቁመዋት አገኘችው ። ስታየው እኔ እንዳልሆንኩ አወቀች ። ታሪኩ ደግሞ ከኔጋር ሲገናኝ ስሟንና ከየት እንደመጣች እየጠቆመ የተፈጠረውን ነገረኝ ። ያኔ ነበር እኔን እየፈለገች እንደሆነ የተረዳሁት ። ቀኑን አላውቅም እንጂ እንደ ማገኛት አውቅ ነበር ። ከሁለት ዓመት በዋላ ያቺን ልጅ ድጋሜ አየዋት ። ቆንጅናዋ እንዳለ ነው ፤ ኧረ እንደውም ይበልጥ ተውባ ነበር ። ተገናኘን ፣ ተቃቀፍን ፣ ለብዙ ሰዓት ቁጭ ብለን አወራን ። ሲመሽብን ስልክ ቁጥር ተለዋውጠን ተለያየን ። ከዛን ቀን አንስቶ ወደ ዱከም እስክትመለስ ድረስ በየቀኑ እንገናኝ ነበር ። ሁለታችንም እንደ በፊቱ ዝምተኛ አልነበርንም ። ስለ ብዙ ነገር አወራን ፣ ተጫወትን ፣ ብዙ ቦታ አብረን ዞርን ። በቃ ባጠቃላይ ፊልም ላይ ወይንም ልቦለድ ላይ የምታውቂውን የፍቅር ህይወት አብረን አሳለፍን ። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የሷን ከንፈር ነበር የሳምኩት ። ወክቱ ክረምት ነበር ፤ የቴዲ አፍሮ "ኢትዮጵያ" አልበም ደግሞ በብዛት ይደመጥ ነበር ። ከሱ አልበም ውስጥ ሁለታችንም "ማራኪዬ" የሚለውን ዘፈን ከቴዲ አፍሮ በላይ ወደድነው ። ልምድ ሆኖብን ሁለታችንም ከዛን በዋላ #ማራኪዬ እያልን መጠራራት ጀመርን ። ማንም ወንድ ቢቀርባት በፍቅር የሚወድቅላት ልጅ ነበረች ። እኔም ወደኩላት ። በጣም ነበር የምንዋደደው ፤ ከምነግርሽ በላይ ። የሚገርምሽ ቀኑን ሙሉ አብረን ውለን ሰለ ማንጠጋገብ ማታ ማታ ደግሞ በስልክ txt እንፃፃፍ ነበር ። እንደውም የሆነ ቀን የተፃፃፍነውን የመልዕክት ብዛት ሳይ #5000 አልፎ ነበር ። እና ማራኪዬ ለኔ ሁሉ ነገሬ ነበረች ። የኔ አሳቢ ፣ የኔ እናት ፣ የኔ ፍቅር ፣ የኔ ረቡኒ ፣ በቃ ምን ልበልሽ ፡ እሷን ምድር ላይ ያሉ ቃላት አይገልጿትም ። በዚች ምድር ላይ እንደሷ የሚወደኝ ፤ እኔም እንደሷ የምወደው አልነበረኝም ። ፍቅርን ምድር ላይ ባሉት ነገሮች ግለፅልኝ ቢሉኝ #ማራኪዬን ነበር የምጠቁመው ። ያን ጊዜ እሷ የ #10ኛ ክፍል matric ፡ እኔ ደግሞ የ #12ኛ ክፍል entrance ፈተና ወስደን ውጤት የምንጠብቅበት ነበር ። ክረምቱን አብረን በፍቅር ዘመትን ። የመጣችሁ ክረምቱን ዘመድ ጋር ለማሳለፍ ነበርና ክረምቱ ሲገባደድ መሄጃዋ ደርሶ በእምባ ተለያየን ። ውጤት ተለቀቀ ፡ ሁለታችንም አለፍን ፡ ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ደረሰኝ ። በስልክ ብቻ በየቀኑ txt እየተፃፃፍን ፡ በሳምንት እየተደዋወልን #8 ወር አለፈ ። ናፍቆታችን ገደቡን ሲያልፍ ቢሾፍቱ መጥቼ እንደማገኛት ቃል ገባሁላት ። በቃሌ መሠረትም ለፋሲካ በዓል ወደ ቤት ስመለስ አንድ ቀን ቀደም ብዬ ከድሬዳዋ ፡ ሸገር ፡ ከዛም ደብረ ዘይት እሷን ላገኛት ሄድኩኝ ። ለሶስተኛ ጊዜ ቢሾፍቱ የሄድኩት ያኔ ነበር ። #27-08-2010 ዓ.ም ። ተገናኘን ፣ በፍቅር ተቃቀፍን ። ስንተያይ እንዴት ደስ እንዳለን ideaw የለሽም ። የሆሳዕና ሳምንት ነበርና የሰራሁላትን የዘንባባ ቀለበት አደረኩላት ። ደብረ ዘይት ላይ አብረን ለ #3 ሰዓታት በፍቅር ሰከርን ። የመጀመሪያው ምሳችንን አብረን በላን ፣ ቢሾፍቱ ሀይቅ ሄደን juice እየጠጣን ተዝናናን ፣ photo ተነሳን ፣ ስለኛ ብዙ ነገር አወራን ፣ ተሳሳምን ፣ ተቃቀፍን ፣ ብቻ ያቺን ቀን በህይወቴ መቼም አልረሳትም ። ስጦታ የአንገት መስቀል አስራልኝ ልባችን እያለቀሰ ተለያየን ። እና አሁን አንገቴ ላይ የምታዪው ይህ መስቀል ማራኪዬ ያን ቀን ያደረገችልኝ ነው' አልኳትና በረጅሙ ተነፈስኩ.....
ምንም ሳትለኝ አልጋው ውስጥ ገብታ ተኛች ። እኔም ከዛን በዋላ አልተናገርኳትም ። እንደ መሸ አልቀረም ፡ ነጋና በጠዋት ተነሳን ። ቁርስ ከበላን በዋላ "እና ደብረ ዘይትን አታስጎበኘኝም ...?" አለችኝ ። 'እሺ' አልኳትና ባቦጋያ ፣ ምሳ ሰዓት ሆራ አርሰዴ ፣ ምሽት ላይ ደግሞ ቢሾፍቱ ሀይቅ ወስጃት ደስ የሚል ቀን አሳለፍን ። ትናንት ማታ በነገርኳት ታሪክ ምክንያት እንደ ከዚህ በፊቱ አትስመኝም ፣ አታቅፈኝም ፣ ሌላው ቢቀር ድንገት አይን ለአይን ስንጋጭ እራሱ አንገቷን ትደፋለች ። ወደ ኩሪፍቱ ተመልሰን እራት ከበላን በዋላ "ማታ ምንም ሳልልህ በመተኛቴ ይቅርታ ። ግን ታሪኩን እንድትጨርስልኝ እፈልጋለሁ" አለችኝ ። እኔም ካቆምኩበት ቀጠልኩላት ። 'እንዳልኩሽ ማራኪዬ ለኔ ሁሉ ነገሬ ነበረች ። ይሄን ደግሞ የፍቅር ታሪኬን ለሚጠይቀኝ ሁሉ አወራ ነበር ። የሆነ ቀን ግን ታሪኬን ከነገርኳቸው ሰዎች መሀል አንዱ "ስለሷ ስታወራ ከልክ በላይ እርግጠኛ የሆንክ ይመስለኛል ። ግን ተስፍሽ አንድ ነገር ልንገርህ ። ከራስህ ውጪ በማንም እርግጠኛ አትሁን ። ሁሉም ሰው አንተ እንደ ምታስባቸው ላይሆኑ ይችላሉ ። እንደዚህ የምልህ ክፉ ነገር አስቤ አይደለም ። ስለ ልጅቷ ከልክ በላይ የተማመንክባት ስለመሰለኝና አንድ ቀን እንዳትጎዳ ስለፈለኩኝ ነው" አለኝ ። በሱ አስተያየት ምንም አልተሸበርኩም ነበር ። እንደውም 'አንተ ማራኪዬን ስለማታውቃት ነው' አልኩት ። ከዛ በዋላ ነው እንግዲህ ጨዋታው የተጀመረው ። "ስማ ተስፍሽ ፡ እንደ ነገርከኝ ከሆነ ማራኪዬ የምትላት ልጅ ፡ አንተ ምንም ብትሆን ፣ የትም ብትሄድ ፣ ሌላው ይቅርና አንተ ብትተዋት እንኳን የማትተውክ ፣ እስከ እለተ ሞቷ ድረስ የምታፈቅርክ የተለየች ሴት ናት ። ይሄን ያክል ደግሞ በሷ እርግጠኛ ከሆንክ ለምን እኔ የምነግርህን ፈተና አታቀርብላትም ...?" አለኝና ፈተናው ምን እንደሆነ ጠየኩት ። ቀጠለና "ምን መሰለህ ፡ #3 ነገሮችን እንድታደርግ እፈልጋለሁ ። #1ኛው ፡ የልደት ቀኗ ሲደርስ ምንም አይነት txt እንዳትልክላት ፣ እንዳት ደውልላትም ። በዚህም ከሁሉ በላይ አንተን ስለ ምትጠብቅህ በጣም ታዝንብሀለች ። #2ኛው ፡ ያንተ የልደት ቀንም ሲደርስ ፡ ከሷ ለሚመጡልህ የመልካም ምኞት መግለጫ መልስ አትስጥ ። ይሄ ነገርም የንዴት መጠኗን ከፍ ያደርጋል ። #3ኛውና ወሳኙ ደግሞ ፡ ክረምት ክረምት እናንተ ጋር ሙገር እንደ ምትመጣ ነግረኸኛል ። እናም ባሁኑም ክረምት መምጣቷ ስለማይቀር ፡ ያኔ ስትገናኙ ፊት ንሳት ፣ እንደ ማትወዳት act አርግ ፣ ከሷ ጋር በመሆንህም ደስተኛ እንዳልሆንክ አስመስል ። አንተን ብላ መጥታ እንደዛ ስትሆንባት መቼም ምን እንደሚሰማት መገመት አይከብድም ። እውነት እልሀለሁ ተስፍሽ እነዚህን ሶስቱን ነገሮች ተግብረህ ፡ ማራኪክ 'እኔ አልተውህም ፣ እንደዚህ ብትሆንብኝም እወድሃለሁ' የምትልህ ከሆነ she is the best girl in the world" አለኝ ። ሶስቱን ፈተና ብሎ የነገረኝን ስሰማ መጀመሪያ ስቄበት ነበር ። እንደ ቀላል አይቼው ፣ እንደ ምታልፈውም በሙሉ ልቤ ስለተማመንኩኝ ልፈትናት ወሰንኩኝ ። ስለዚህ ጉዳይ ከኔና ከልጁ ውጪ ማንም ሰው አያውቀውም ። ደስ የሚለው ነገር የልደቷ ቀን ያኔ የነበርንበት ወር ውስጥ ነበር ። የመጀመሪያው የፈተና ቀን ደረሰ ፡ የልደቷ ቀን....


ይ................
ቀ..................
ጥ...................
ላ....................
ል....................
🌺የከንቲባው ልጅ🌺

🔥ክፍል 14


.
.
.
ብዙም አልተኛሁም ነበር ። በትካዜና በሀዘን እንደ ዳግም ምፅአት የራቀኝ ለሊት ነጋ ። የኔስ ይሁን የራሴ ችግር ነው ። የከንቲባውን ልጅ ግን ለማዝናናት ይዤ መጥቼ ቀኗን አበላሸሁ ። ጠዋት ከእንቅልፍ ሳይሆን ከአልጋው ላይ ስነሳ "ደና አደርክ የኔ ጌታ ፡ ቁርስ ቀርቧል እሺ ቶሎ ፊትህን ታጥበህ ና" አለችኝ ። ቁርሱን ከበላን በዋላ 'ትናንት እንደዛ ስለ ሆንኩብሽ በጣም ይቅርታ' ስላት "ኧረ አያሳስብም ፡ እኔ ከዛ በላይ ሆኜብህ አልነበር እንዴ ፡ ባይሆን ካሁን በዋላ እንደዛ አትሁን እሺ ፡ የሰውን እምባ ጠርገው እያሳሳቁ የምን ለራስ ማልቀስ ነው ...?" አለችኝ በአሽሙር መልክ ። ቀጥላም "ካሁን በዋላ እንደውም ከቴዲ አፍሮ ሙዚቃ #ማራኪዬ የሚለውን ሳይሆን #መማፀኔ የሚለውን መውደድ ያለብክ ይመስለኛል" አለችኝና ድምጿን ከፍ አድርጋ ዘፈኑን ታዜምልኝ ጀመር ።

"በደለኛ ሰው ይቅርታ ብሎ አንሶ ሰው ከካሰ ፡
ይኖር ወይ ልቡን ያልመለሰ ፣
ሳይገባኝ ለኔ ፡ የቱጋ እንደሆን እንኳን ማስቀየሜ
ተይ ብያት ነበር ባለኝ አቅሜ ።
መማፀኔ ፡ ማሪኝ ማለቴ ፡
ለኔስ ሳይገባኝ ነው ጥፋቴ ፣
ታድያ እንዴት ይሆን ፡ ወዳጅን ነግሮ ፡
ልብን መመለስ ወደ ድሮ" ።

ቆሜ ነበር ያጨበጨብኩላት ። ስትዘፍን ድምጿ ስያምር ። በቃ ሴቷ ቴዲ አፍሮ ብያታለሁ ። "ከቤት ስለማልወጣ ስዕልና ሙዚቃ እቤት ውስጥ እሞክራለሁ ። እስካሁን አባቴ ከሰጠኝ ስጦታዎች መካከል በጣም የምወደው ጊታር'ን ነው ። ሲከፋኝና ብቸኝነት ሲሰማኝ በጊታሬ እዘፍናለሁ ። አንተ ከመጣህ ወዲህ ብቸኝነት ስላልተሰማኝ ነው እሺ ጊታሩን አውጥቼ ያልተጫወትኩት" አለችኝ እያሾፈችብኝ ። ከዛን "ስማኝማ ፡ ዛሬ ማክሰኞም አይደል ፡ ደብረ ዘይት ላይ የመጨረሻ ቀናችን እኮ ነው ። ታውቃለህ አባዬ ባለፈው ሀሙስ ነበር ሳምንት እመለሳለሁ ብሎ የሄደው ። እና ሳምንቱ ደግሞ ከነገ ወዲያ ስለሆነ ነገ ወደ ድሬዳዋ መመለስ ይኖርብናል" አለችኝ ። በግልጽ ባትነግረኝም ለማለት የፈለገችው ነገር ገብቶኛል ። የዙሪያ ጥምጥሙ ፍቺ ፈታ እንበል የሚል መሆኑ ነው ። ከዛ በፊት ግን ልጠይቃት ብዬ የረሳሁትን ነገር የአባትዋን ስም ስታነሳ ትዝ አለኝ ። 'ስሚማ ፡ አባትሽ ግን ለምን ይሄን ሁሉ ዓመት ለብቻሽ በአንድ ቤት ውስጥ እንዳስቀመጠሽ እኮ በግልጽ አልነገርሽኝም...? ፡ ማለቴ አባትሽ በስልጣኑ ምክንያት ከሰዎች ጋር ችግር ውስጥ ገብቶ አንቺላይ ጥቃት እንዳይደርስ ከፈራኮ አንቺን በአንድ ቤት ውስጥ ከማስቀመጥ ይልቅ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ይችል ነበር ' አልኳትና ጠየኳት ። እሷም "የመጀመርያው ፡ አባቴ ብቻውን ስላሳደገኝ ፣ ከኔ ውጪ ማንም ስለሌለውና ከኔ ተለይቶ መኖር ስለማይችል ነው ። ሁለተኛው ፡ ውጪ ቢልከኝም እዛ ማንም ስለሌለን ከፈረንጅ ነፃነት የሀገር ውስጥ እስረኛ መሆን ይሻላል ብሎ ነው ። ያው 'ከማያውቁት መላክ ፡ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል' ይባልም የለ ። ሲጀምር እሱ ሂጂም ቢለኝ ከሱ ተለይቼ ውጪ ሀገር መኖር አልፈልግም" አለችኝና ሶስተኛው ብላ ልትቀጥል ስትል 'ኧረ ይበቃል ፡ ሶስተኛ ፣ አራተኛ እያልሽ ከቀጠልሽማ ሳንዝናና መሽቶ መንጋቱ ነው' አልኳትና ይዣት ተነሳን እና ከአንዱ ምግብ ቤት ገብተን ምሳ ከበላን በዋላ "ፍቅር ግን ለአንተ ምንድነው...?" አለችኝ የከንቲባው ልጅ በልጅቷ የቅድሙ መልስ እንደኔው ተገርማ ። 'እርግጠኛ ነኝ ሁላችንም ብያንስ አንድ ጊዜ አፍቅረናል ። እንደውም አብዛኞቻችን የፍቅርን ትርጉም ሳናውቅ ነው ያፈቀርነው ። anyways ፍቅር ግን ለኔ ...! አንድ ወንድና ሴት ተፈላልገው የሚመሰርቱት ግኑኝነት ...? ፡ እሱ ነው ፍቅር ...? ፡ አይመስለኝም ። እስቲ ወይ የራስሽን ወይንም ደግሞ የጓደኛሽን የፍቅር ታሪክ ለትንሽ ደቂቃ አስቢው ። እያሰብሽው እንደሆነ ተስፋ አለኝ ። እርግጠኛ ሆኜ የምነግርሽ እራሳችንን ወደን እንጂ ሰውን አፍቅረን አናውቅም ። እንዴት...? ለምትዪኝ :- በመጀመሪያ ወንድ ከሆነ አንዲት ሴትን ፡ ሴት ከሆነች ደግሞ የሆነ ወንድ ፡ በሆነ አጋጣሚ ያገኛሉ ። የሆነ ነገሯ ይማርከዋል ፡ #90% መልኳ ፣ አካሄድ ፣ አለባበስ ፣ አነጋገር ፣ ወዘተ ። ይተዋወቃሉ ፡ ሊግባቡም ላይግባቡም ይችላሉ ። ጉዳዩ እሱ አይደለም ። ከጥቂት ቀናት በዋላ ፡ ካላገኘዋት ፣ እጄ ካላስገባዋት ፣ የኔ ካልሆነች ፣ ህይወቴ ካለሷ ባዶ ነው ፣ ወዘተ ማለት ይጀምራል ። እዚህ ጋር ልብ በይ እንግዲህ ። አነዚህን ነገሮች እያለ ያለው ለልጅቷ አስቦና ተጨንቆ አይደለም ፡ ለራሱ ፍላጎት እንጂ ። ስለናፈቀችው ፣ ደስ ስላለችው ፣ ስለምታምር ፣ ከሷ ጋር ከሆነ ደስተኛ እሆናለሁ ብሎ ስለሚያስብ ፣ ባጠቃላይ ልጅቷ ትሆነኛለች ብሎ እንጂ ፡ ለልጅቷ እሆናታለው ፣ ብሎ አይደለም ። አስተውይ ፡ መጀመሪያ ላይ አፈቀርኳት ብሎ ሲያወራ የሱ ህይወት ካለሷ ባዶ ሆኖ ስለተሰማው እንጂ የሷ ህይወት አሳስቦት አይደለም ። የሱ ጭንቀት እንጂ የሷ ፍላጎት አልታየውም ፤ አያውቅምም ። በቃ በዛ ሰዓት እሱ የሚፈልገው ነገር ቢኖር ልጅቷ የሱ እንድትሆን ነው ። የሱ ብቻ ። እሷ እንኳን የሌላ ሰው ሆና ማየቱ ይቅርና ሰላም እንኳን ቢሏት ካልገደልኳቸው ሊልም ይችላል ። እሷን ከራሱ ውጪ ከሌላ ሰው ጋር ለሴኮንድ እንኳን ማሰብ አይፈልግም ። እሷ አልፈልግህም ብትለው እንኳን በግድ ካልሆንሽ የሚል ጉድ ውስጥም ሊገባ ይችላል ። አስቢ ይሄን ሁሉ እያደረገ ያለው ለራሱ ሲል ነው ። ይሄንን ነው እንግዲህ ፍቅር ብለን የጠራነው ። እመኚኝ ግን ከዚህ ሰው በላይ እራስ ወዳድ ሰው በምድር ላይ የለም ። የፍቅር ትርጉም ግን ይህ አልነበረም ። ፍቅር ከራስ አልፎ ለሰዎች ሁሉ መኖርና መሞት ነው ። ቢተያዩም ባይተያዩም ፣ ብታምርም ባታምርም ፣ ለሱ ህይወት አስፈላጊ ሆነች አልሆነች ፣ እውነተኛ ልብ ካለው ያኔ የእውነት ፍቅር ከልቡ ይገባል ። በአይኑ ሳይሆን በልቡ ማየት ሲጀምር እሱ ሳይፈልገው ቤቱ ድረስ መጥቶለት ደጁን ያንኳኳል ። አፍቃሪ መሆን ከፈለገ ከልቧ ውጪ ምኗንም ሳያይ ፣ ምንም ሳታደርግለት ፣ ብትበድለው ብትክሰው ፣ ለሱ ሆነች አልሆነች ፣ ባጠቃላይ የሷ ነገር አሳስቦት እንጂ የሱ ጎዶሎነት ተሰምቶት አይውደድ ። ለጎዶሎው ብሎ ካፈቀረ አንድ ቀን እንዳልተሟላለት አስቦ ሊተዋት ይችላል ። የሷን ጎዶሎ ሊሞላ ቢሯሯጥ ግን አትራፊ ይሆናል ። ቅዱሱ መፅሐፍም "ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" አይደል የሚለው ። ክርስቶስስ ከሰማይ ላይ ወርዶ የሰውን ስጋ የለበሰው ለራሱ ጥቅም ይመስልሻል ...? ፍቅር መጠቀም ሳይሆን መጥቀም ነው ። እውነተኛ አፍቃሪ በነገሮች ሁሉ ቅድምያ ለራሱ ሳይሆን ለሌላ ሰው ሰጥቶ የሚጠቅም እንጂ የራሱን ችግር ለማሸነፍ ብሎ በሌሎች የሚጠቀም አይደለም...
"አንተ ልጅ ግን ሰባኪ ነገር ነህ እንዴ ...?" አለችኝ ሳወራላት የነበረውን ሁሉ በተመስጦ አይን አይኔን ትኩር ብላ እያየችኝ ከሰማችኝ በዋላ ። ቀጥላም "ቆይ ግን አንተ ሴት ልጅን መተህ አታውቅም ...?" አለችኝና ብዙ ዓመት ወደዋላ እንድመለስ አረገችኝ ። 'ትዝ ይለኛል እንደ ትናንት ፡ ከ #10 ዓመት በፊት በ #2001 ዓ.ም #4ኛ ክፍል እያለሁ ነበር ። #6ኛውን period ተምረን ተደወለ ። ምሳ ሰዓት በመሆኑ ፣ እቤታችንም ለት/ቤቱ ቅርብ ስለነበረ ወደ ቤት ለመግባት ቦርሳዬን ይዤ ከ desk ላይ ተነሳሁ ። ነገር ግን አጠገቤ ትቀመጥ የነበረችው አቢጊያ የምት